ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ቅርንጫፍ
Статистика- Последний пост
- 14 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 151
- Всего постов
- 155
- Тип
- открытый
- Язык
- und
- Категория
- Новости и СМИ (по похожим)
- В каталоге с
- 12 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 100
- 1/48двое суток
- 114
- 1/72трое суток
- 123
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
"የጠፈር ተመራማሪና የሶፍትዌር እንጂነር መሆን እፈልጋለሁ።" በ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና 100 ያመጣችው የኮምቦልቻ ከተማዋ እንቁ ተማሪ ነጅዋ ሰይድ እና ወላጅ አቧቷ ከፋና ሚዲያ ከርፖሬሽን ጋር በስልክ ያደረጉት ቆይታ። ትኩስ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ፋና ኤፍ ኤም 96.0 ቴሌግራም ፦ https://t.me/dessiefana ፊስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=10007995035
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
የክልሉን ገጽታ የሚያንጸባርቁ ደማቅ በዓላት በቀጣይ ሳምንት ጀምረው ይከበራሉ። ደሴ- ነሐሴ 08/2018/ደሴ ፋና/ የክረምት ክብረ በዓላት በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች በድምቀት እንደሚከበሩ የአማራ ክልል ባህል ቱሪዝም እና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ መልካሙ ጸጋዬ ገልፀዋል። ክብረ በዓላቱ ባህላዊ ይዘታቸውን ጠብቀው እንዲከበሩ ድጋፍና ክትትል ይደረጋል። የቢሮ ኃላፊው አክለውም ክብረ በዓላቱ በተለያዩ አካባቢዎች በባህል አልባሳት፣ የፀጉር አሰራር እና በልጃገረዶች ጨዋታ ከተከበሩ በኋላ በክልል ደረጃ የማጠቃለያ ፕሮግራም በባህር ዳር ከተማ በከፍተኛ ድምቀት ይከበራል ብለዋል። በዓላቱም ቡሄ፣ሻደይ፣አሸንድዬ፣ሶለል፣አሱሪቴ፣እንግጫ ነቀላ እና ከሴ አጨዳ መሆናቸውን ሃላፊው አስታውቀዋል። አማራ ኮሙኒኬሽን ትኩስ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ፋና ኤፍ ኤም 96.0 ቴሌግራም ፦ https://t.me/dessiefana ፊስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=10007995035
без подписи
без подписи
ኤርሊንግ ሀላንድ በአራት ክብረወሰኖች የጊነስ ድንቃ ድንቅ መዝገብ ላይ ሰፈረ። ደሴ- ነሐሴ 08/2018/ደሴ ፋና/የማንቸስተር ሲቲው አጥቂ ኤርሊንግ ሀላንድ በክለብ እና በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ያስመዘገባቸውን የግብ ስኬቶች ተከትሎ አራት የጊነስ ዓለም ድንቃ ድንቅ መዝገቦች (Guinness World Records) ሰርተፊኬት ተበረከቱለት። የ26 ዓመቱ ኖርዊያዊ አጥቂ አዲሱ የውድድር ዓመት ከመጀመሩ በፊት የጊነስ የክብር ሰርተፊኬቶቹን የተረከበ ሲሆን፣ በፕሪሚየር ሊግ፣ በሻምፒየንስ ሊግ እና በኔሽንስ ሊግ ያስመዘገባቸው ድንቅ ስኬቶች ለዚህ ዕውቅና አብቅተውታል። ሀላንድ በ111 ጨዋታዎች 100 የፕሪሚየር ሊግ ግቦችን በማስቆጠር በውድድሩ ታሪክ በፍጥነት እዚህ ደረጃ የደረሰ ተጫዋች ሆኗል። በተጨማሪም በማንቸስተር ሲቲ የመጀመሪያ የውድድር ዘመኑ 36 ግቦችን በማስቆጠር በአንድ የፕሪሚየር ሊግ ዘመን ከፍተኛ ግብ ያስቆጠረ ተጫዋችም ተሰኝቷል። በኔሽንስ ሊግ ደግሞ 19 ግቦችን በማስቆጠር የውድድሩ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ሲሆን፣ በሻምፒየንስ ሊግ ውድድር ከአርቢ ላይብዢግ ጋር በተደረገ ጨዋታ አምስት ግቦችን በማስቆጠር በአንድ ጨዋታ ብዙ ግብ በማስቆጠር ከሊዮኔል ሜሲ እና ሉዊዝ አድሪያኖ ጋር ክብረወሰኑን ተጋርቷል። እነዚህ ስኬቶች ሀላንድን ከዓለም እግር ኳስ ከፍተኛ የግብ አስቆጣሪዎች መካከል አስመድበውት፤ በጊነስ የድንቃ ድንቅ መዝገብ ስሙ እንዲሰፍር አድርገውታል። ትኩስ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ፋና ኤፍ ኤም 96.0 ቴሌግራም ፦ https://t.me/dessiefana ፊስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=10007995035
без подписи
без подписи
без подписи
በክልሉ ጤና ቢሮ በጀት የተያዘለት የደሴ የአዕምሮ ጤና ህክምና ማዕከል ግንባታው በጥሩ አፈጻጸም ላይ ይገኛል። ደሴ- ነሐሴ 08/2018/ደሴ ፋና/ ፕሮጀክቱ በደሴ ከተማና አካባቢው ለሚገኙ የአእምሮ ጤና ችግር ላለባቸው ወገኖች የተሟላ ሕክምና እንዲያገኙ ማድረግ የሚያስችል ፕሮጀክት ነው። የስነ-አዕምሮ ህክምናን ከመደበኛ የጤና አገልግሎቶች ጋር በቅንጅት መስጠት፣ ተኝቶ እና ተመላላሽ ታካሚዎችን በመቀበል ማገገሚያ አገልግሎቶችን መስጠት የሚያስችል ነው። ፕሮጀክቱ ተዟዙረው የጎበኙት የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ አበበ ተምትሜ ማዕከሉ በተለያየ ምክንያት ለአእምሮ ህመም የተዳረጉ ዜጎች ጤንነታቸው እስኪመለስ የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል ነው ብለዋል። ፕሮጀክቱ ደረጃውን የጠበቀ የአእምሮ ህክምና መስጫና የማገገሚያ ማዕከል መሆኑንም አስረድተዋል። የደቡብ ወሎ ዞን መንግስት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ትኩስ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ፋና ኤፍ ኤም 96.0 ቴሌግራም ፦ https://t.me/dessiefana ፊስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=10007995035
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
በቃሉ ወረዳ የክረምቱን የዝናብ እጥረት ለመቋቋም የሚያስችል የእርጥበት እቀባ ሥራ በሕዝብ ንቅናቄ እየተከናወነ ነው የክረምት የዝናብ እጥረት በሰብል ልማት ላይ የሚያሳድረውን ተጽዕኖ ለመቋቋም እንዲያስችል በደቡብ ወሎ ዞን በቃሉ ወረዳ የእርጥበት እቀባ ሥራ በሁሉም ቀበሌዎች በሕዝብ ንቅናቄ እየተሠራ ይገኛል። ደቡብ ወሎ ኮምንኬሽን ትኩስ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ ለማግኘት ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ደሴ ፋና ኤፍ ኤም 96.0 ቴሌግራም ፦ https://t.me/dessiefana ፊስቡክ፦https://www.facebook.com/profile.php?id=10007995035
без подписи
без подписи