DW Amharic
Статистикаይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።
- Последний пост
- 15 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 51
- Всего постов
- 177
- Тип
- открытый
- Язык
- ti
- Категория
- Новости и СМИ (по похожим)
- В каталоге с
- 12 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 2 933
- 1/48двое суток
- 3 361
- 1/72трое суток
- 3 624
Медиана по постам, которые мы застали свежими и померили через сутки.
Посты
без подписи
без подписи
https://tinyurl.com/njvu8f9s
https://tinyurl.com/yc4euedm
https://tinyurl.com/4zyhky6f
https://tinyurl.com/3fs4xwum
https://tinyurl.com/mpm2sw4e
https://p.dw.com/p/5IpL4?at_medium=Messenger&at_campaign=Telegram&at_channel=DW_Amharic&at_dw_language=am
https://p.dw.com/p/5IrGB?at_medium=Messenger&at_campaign=Telegram&at_channel=DW_Amharic&at_dw_language=am
Live stream finished (1 hour)
Live stream started
የስርጭት ማስታወቂያ የተከበራችሁ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ የሚጀምረው የነሐሴ 8 ቀን፣ 2018 ዓ.ም. የዶቼ ቬለ ቀጥታ ሥርጭት በሚከተሉት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የተጠናቀሩ ዘገባዎች፤ የጋዜጠኞች መብት ተማጋቹ ድርጅት ሲፒጄ የኢትዮጵያ መንግስት በጋዜጠኞች ላይ የሚደርሰውን ጫና ማውገዙ ኢትዮጵያውያን በሚያዘወትሩት ምሥራቃዊ የፍልሰት መስመር ባለፉት አምስት ወራት ብቻ 106 ስደተኞች መሞታቸውን የተባበሩት መንግሥታት የፍልሰተኞች መርጃ ድርጅት መግለፁን፣ የኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ድርጅት የዜጎች መብት እንዲከበር የሚቀርባቸው ሃሳቦች አለመተግበሩ እንዳሳሰበው መግለፁ በኢትዮጵያ በሴቶች ላይ የሚፈጸመው ጥቃት ብሔራዊ ቀውስ ሆኖ እንዲታውጅ የመብት ተሟጋቾች ማሳሰባቸውን፣ እንዲሁም በኢትዮጵያ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ የቻይና እና የአሜሪካ ኩባንያዎች ፉክክርን ያስቃኛሉ። ዶቼ ቬለ ለመከታተል በሳተላይት፣ በኢትዮ ሳት ወይንም (NSS-12) በ10,985.0 ሜጋ ኸርዝ፣ ሆሪዞንታል፣ DW-08 ላይ ፈልጉን። ትራንስፖንደሩ፦ MEH 01 ወይንም EAH 01 ነው። DW Amharic በተባለው መተግበሪያ ከድረገጻችንም ስርጭቱን በቀጥታ ሲተላለፍ ማድመጥ ይቻላል። DW Amharic እያላችሁ በመግባትም ከፌስቡክ፤ ቴሌግራም እና ዩቲዩብ ገጻችንም ተከታተሉ፤ ቤተሰብ ሁኑ፤ ለሌሎችም አጋሩ። እናመሰግናለን
ከዩናይትድ ስቴትስ የሚባረሩ ሰዎችን ለመቀበል የሚስማሙ የአፍሪቃ አገራት ቁጥር እየጨመረ ነው። የተቀባይ አገራቱ ደጋፊዎች ኹኔታው ተግባራዊ መፍትኄ ያበጃል ይላሉ፥ ተቺዎች በበኩላቸው ፍልሰተኞች በግዳጅ ለመባረራቸው መጠቀሚያ ኾነዋል ሲሉ ይሞግታሉ።#africaexplained
እራስ ገዟ የሶማሊያ ግዛት ፑንትላንድ የሱማሊያው ፕሬዝደንት ሀሰን ሼኽ መሀሙድ ጋልካዮ ከተማን እንዳይጎበኙ አስጠነቀቀች። የፑንትላንድ የድረገጽ የመረጃ ምንጮች እንደሚሉት የፑንትላንድ አስተዳደር የሶማሊያው ፕሬዝደንት በማዕከላዊ ሙዱግ ግዛት የምተገኘውን ቁልፍ ከተማ ጋልካዮችን ለመጎብኘት ማቀዳቸውን ተከትሎ ሠራዊቱ በተጠንቀቅ እንዲቆም እንደሚያደርግ አስታውቋል። የፑንትላንድ አስተዳደር የሶማሊያ ፕሬዝደንት መሀሙድ ወደ ጋልካዮ ለጉብኝ የመምጣታቸው ምስጢት በሰሜን ምሥራቅ የሶማሊያ ግዛት አካባቢ ግጭት ለመቀስቀስ ያለመ ዘመቻ ነው ብሎታል። አያይዞም፤ «የቀድሞው የፌደራሉ መንግሥት ፕሬዝደንት ሀሰን ሼኽ መሀመድ ፑንትላንድ ላይ ግጭት ለመፍጠር ጥረታቸውን አላቋረጡም» ያለው የፑንትላንድ አስተዳደር በመግለጫው፤ የፕሬዝደንት መሀሙድን ጋልካዮን የመጎብኘት እቅድ ተቃውሟል። እንዲያም ሆኖ የፑንትላንድ ባለሥልጣናት ያቀረቡትን ክስ የሚያጠናክር ማስረጃ አላቀረቡም። የሶማሊያው ፕሬዝደንት ግን፤ የፌደራሉ መንግሥት ከየትኛውም ግዛት ጋር የፖለቲካ ልዩነቶች ቢኖሩም እንኳ ግጭት ውስጥ እንዳልገባ መናገራቸው ተገልጿል። የፑንትላንድ ማስጠንቀቂያ የተሰማው፤ የእራስ ገዟ ኃይሎች በሰሜን ጋልካዮ ወታደራዊ የጦር ሰፈር ላይ ከፌደራሉ መንግሥት ወታደሮች ጋር ኃይለኛ ውጊያ አድርገው፤ ከአንድ መቶ በላይ ተዋጊዎችን ማሰራቸውን ይፋ ማድረጉን ካሳወቀ ከሳምንታት በኋላ መሆኑ ነው። ፑንትላንድ በጎርጎሪዮሳዊው 2024 ዓ.ም. የሶማሊያ ፓርላማ አወዛጋቢውን የሕገ መንግሥት ማሻሻያዎች ካደረገ በኋላ ለፌደራል መንግሥት ተቋማት የሰጠችውን እውቅና ማንሳቷን አስታውቃለች።
... CPJ አያይዞም 300 ፖለቲከኞች፤ ጋዜጠኞች እና ሌሎች በአማራ ክልል ካለው ግጭት ጋር በተገናኘ በሽብር ወንጀሎች የተከሰሱ የይቅርታ ደብዳቤ እንዲፈርሙ መጠየቃቸውን መገናኛ ብዙኃን መዘገባቸውን ጠቅሷል። እንደ CPJ መግለጫ ባለፈው የየካቲት ወር ፍርድ ቤቱ በጋራ የሚታየው የጎበዜ፤ መስከረም፤ ገነት እና ዳዊት ጉዳይ በቂ መረጃ እንዳለው እና የፍርድ ሂደቱም እንደሚቀጥል መግለጹን፤ በተደጋጋሚም ቀጠሮው በመለወጡ ጉዳያቸው ዘግይቶ ለመጪው ኅዳር 10 ቀን 2019 ዓ.ም. መቀጠሩን አመልክቷል። አባይን በተመለከተ ግን አቃቤ ሕጎች በቂ መረጃ እንዳላቸውና ጉዳዩም መታየት ስለመቀጠሉ ለመወሰን በመጪው ጥቅምት 6 ቀን 2019 ዓ.ም. መቅጠሩንም ገልጿል። ጋዜጠኞቹ በቀረበባቸው ክስ ጥፋተኛ ከተባሉ የእድሜ ልክ እስራት እንደሚጠብቃቸውም ጠቁሟል። መንግሥት ከእስር ለመለቀቂያ ሂደት ብሎ ለጋዜጠኞቹ ያቀረበላቸው ሃሳብ «ምሕረት» የሚል ቢሆንም፤ ጠበቃ ሰሎሞን ለCPJ እንደተናገሩት፤ በኢትዮጵያ ሕግ ይቅርታ የሚሰጠው፤ ተከሳሾች በቀረበባቸው ክስ ጥፋተኛነታቸው ተረጋግጦ የመጨረሻው የፍርድ ውሳኔ ከተሰጠ በኋላ ነው። የአምስቱ ጋዜጠኞች የፍርድ ሂደት ገና ባለመጠናቀቁ ጉዳያቸው አንድም ክሱን በማንሳት አለያም በይቅርታ ሊቋጭ እንደሚገባ ጠበቃው መግለጻቸውን CPJ ጠቅሷል። CPJ ስለጉዳዩ ከፍትህ ሚኒስቴር እና የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ቢሮ ምላሽ ለማገኝነት በኢሜይል መጠየቁን፤ ሆኖም መልስ እንዳልተሰጠው ገልጿል። ለፌደራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽንም ኢሜይል ለመላክ ሞክሮ እንዳልተሳካለትም አስታውቋል።
ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች CPJ ኢትዮጵያ ውስጥ በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞች የተከሰሱበትን «የሽብር ወንጀል» አምነው ይቅርታ እንዲጠይቁ ተደርጎባቸዋል ያለውን ግፊት አወገዘ። ለጋዜጠኞች መብት የሚሟገተው ተቋም የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ላለፉት ሦስት ዓመታት ፍትህን እየጠበቁ በእስር ቤት የሚገኙትን አምስት ጋዜጠኞች ነጻነታቸውን ለማግኘት በግጭት ውስጥ ተሳትፎ እንደነበራቸው አምነው ይቅርታ እንዲጠይቁ ከማስገደድ ይልቅ ባስቸኳይ እንዲለቀቁ ትናንት ባወጣው መግለጫ ለኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ጥሪው አቅርቧል። በአማራ ክልል በተቀሰቀሰው አለመረጋጋት ላይ በሠሯቸው ዘገባዎች ምክንያት አምስቱ ጋዜጠኞች የሽብርተኝነት ክስ ተመሥርቶባቸው የታሠሩት ከሦስት ዓመታት ገደማ በፊት እንደነበር ተቋሙ አስታውሷል። የጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ፤ መስከረም አበራ፤ ገነት አስማማው፤ ዳዊት በጋሻው እና አባይ ዘውዱ ጠበቃ የሆኑት ሰሎሞን ገዛኸኝ ለCPJ እንደገለጹት እስረኞቹ የተጠየቁትን «እራሳቸውን ወንጀለኛ የሚያደርግ» የይቅርታ ደብዳቤ አንጽፍም ብለዋል። አክለውም ጠበቃው የእስር ቤት ሀላፊዎች ደንበኞቻቸው በጋዜጠኝነት መሥራት እናቆማለን የሚል ቃል ገብተው ጭምር የተባለውን ደብዳቤ እንዲጽፉ፤ እንዳስፈራሯቸው እና ከሌሎች እስረኞች እንደነጠሏቸውም መግለጻቸው ተጠቅሷል። «እነዚህን አምስት ጋዜጠኞች ለዓመታት እስር ቤት ካቆዩ እና ፍርዳቸውን ካዘገዩ በኋላ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት አሁን አስገድደው በፍርድ ቤት አልፈጸምንም ያሏቸውን ወንጀሎች ጭምር እንዲያምኑ ግፊት ያደርጋሉ» ያሉት CPJ የአፍሪቃ ፕሮግራም አስተባባሪ ሙቶኪ ሙሞ፤ የጋዜጠኞቹን ስም ዘርዝረው ባለሥልጣናቱ እነሱን ለማዋረድ እና ለማታለል ያደርጋሉ ያሉትን ጥረት በማውገዝ እንዲለቀቁና የጋዜጠኝነት ሥራቸውን እንዲሠሩ ጠይቀዋል።...
https://p.dw.com/p/5IlJo?maca=amh-RED-Telegram-dwcom አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
https://p.dw.com/p/5IlvZ?maca=amh-RED-Telegram-dwcom አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
https://p.dw.com/p/5Im26?maca=amh-RED-Telegram-dwcom አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
https://p.dw.com/p/5ImCL?maca=amh-RED-Telegram-dwcom አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot