Fresh መረጃ | FreshNews
СтатистикаFresh መረጃ ታማኝ የመረጃ ምንጭ፣ ብቃት ባላቸው ጋዜጠኞች ተዘጋጅቶ የሚቀርብ፣መረጃዎችን በትኩሱ የሚያደርስ የዜና ቻናል ነው ። ሀሳብ ፣ አስተያየት ፣መረጃ ለማጋራት ፣ማስታወቂያ ለማሰራት ያናግሩን።👇👇 @Freshes_newsbot Fresh News,Fresh Updates.
- Последний пост
- 17:18
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 68
- Всего постов
- 68
- Тип
- открытый
- Язык
- ti
- Категория
- Новости и СМИ
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 1 413
- 1/48двое суток
- 1 619
- 1/72трое суток
- 1 746
Медиана по постам, которые мы застали свежими и померили через сутки.
Посты
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
ብስኩት ልግዛልሽ ብሎ በማታለል የ5 ዓመት ህፃን ልጅን አስገድዶ የደፈረው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ። በሀላባ ዞን በሀላባ ቁሊቶ ከተማ ዛላ ፍሬ ቀበሌ ደነቤ ፋማ ቀጠና ልዩ ስፍራ ነው የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው፡፡ ተከሳሽ በሀሩ ሽርሞሎ የተባለ ሲሆን የ5 ዓመት ህፃን ልጅ የሆነችውን ግለሰብ በግምት ከቀኑ 11:00 ሰዓት በሚሆንበት ጊዜ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ ዛላ ፍሬ ቀበሌ ደነቤ ፋማ ቀጠና ልዩ ስፍራው ደነቤ ተብሎ በሚጠራበት ስፍራ ብስኩት እገዛልሻለሁ ብሎ በማታለል የአስገድዶ መድፈር ወንጀል መፈፀሙን የዞኑ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ኑርዬ ከድር ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል። ፖሊስ ግለሰቡ በተጠረጠረበት የግብረ ስጋ ድፍረት በደል መፈፀም ወንጀል የምርመራ መዝገቡን አጠናቆ ለሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ዐቃቤ ህግ ያስተላልፋል፡፡ ተከሳሽ ወንጀሉን አልፈፀምኩም ብሎ ክዶ የተከራከረ ሲሆን ዐቃቤ ህግ የሰውና የሰነድ ማስረጃ በማቅረብ ከሰማ በኃላ ተከሳሽ እንዲከላከል ብይን ቢሰጥም የቀረበበትን የወንጀል ክስና ማስረጃ ማስተባበል ባለመቻሉ በተከሰሰበት የወንጀል ህግ ጥፋተኛ ተብሏል ። በዚህም የሀላባ ቁሊቶ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድቤት ተከሳሹ በተከሰሰበት የወንጀል ክስ በ14 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ዉሳኔ ማስተላለፉን ኮማንደር ኑርዬ ከድር ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet
የመንግሥት «ሥልጣንን የማዕከላዊ ማድረግ» ጥረት በ2025 የኢትዮጵያን ዲሞክራሲያዊ ተቋማትና ሰብአዊ መብቶች አዳክሟል — የአውሮፓ ሕብረት የኢትዮጵያ መንግሥት በብሔር ውጥረቶች እና በትጥቅ ታጣቂዎች እንቅስቃሴ መካከል ሥልጣንን የማዕከላዊ ለማድረግ ያደረገው ጥረት በ2025 «ዲሞክራሲያዊ ተቋማትን ይበልጥ ያዳከመ እና የሰብአዊ መብቶች መከበርን የሸረሸረ» እንደነበር የአውሮፓ ሕብረት የ2025 ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች እና የዲሞክራሲ ሪፖርት ይፋ አደረገ። ሪፖርቱ፤ የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት እና የዲሞክራሲ ሁኔታ በትግራይ፣ በአማራ እና በአፋር ክልሎች ለሁለት ዓመታት በተካሄደው አውዳሚ ጦርነት ያልተፈቱ መዘዞች፣ የትጥቅ ግጭቶች እና አለመረጋጋቶች ተጽዕኖ ስር መቆየቱን ጠቁሟል። በአፋር እና በአማራ ክልሎች ሰፊ ውጊያዎች የቀጠሉ ሲሆን፣ በኦሮሚያ እና በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎችም የፀጥታ ችግር መቀጠሉን ገልጿል። በተጠቀሰው ዓመት ትጥቅ በመፍታት፣ በሽግግር ፍትሕ እና በተጠያቂነት እርምጃዎች ላይ የተፈጠሩ መዘገየቶች እንደነበሩና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን የሚደረጉ ሰፊ ጥረቶችን ማስተጎጎላቸው በሪፖርቱ ተጠቅሷል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet
የእስራኤል ጦር በደቡብ ሊባኖስ የሚያካሂደው የቦምብ ድብደባ ቀጥሏል። የሊባኖስ ብሔራዊ የዜና ኤጀንሲ እንዳስታወቀው፣ የእስራኤል ኃይሎች በደቡብ ሊባኖስ በሚገኙ በርካታ መንደሮች እና ከተሞች ላይ የቦምብ ድብደባ እና የውድመት ዘመቻቸውን ቀጥለዋል። የእስራኤል ኃይሎች በአካባቢው ሰዓት አቆጣጠር ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት ገደማ በማሻ አል-ማንሱሪ አካባቢ ከፍተኛ ፍንዳታ ማድረሳቸውን NNA ዘግቧል። በተጨማሪም በማጅዳል ዙን ፣ አል-ማንሱሪ እና በአቅራቢያው በሚገኙ ሸለቆዎች የማሽን ጠመንጃ ተኩስ እንደነበር ተዘግቧል። የእስራኤል የጦር አውሮፕላኖች እና ድሮኖች አሁንም በአየር ላይ በረራቸውን እንደቀጠሉ ዘገባው አክሎ ገልጿል። ፍንዳታዎቹ የእስራኤል ታንኮች በቢንት ጅቤል ወረዳ ወደምትገኘው ሃዳታ ካደረጉት እንቅስቃሴ ጋር በተመሳሳይ ጊዜ የተከሰቱ መሆናቸውን ዘገባው ጨምሮ ገልጿል ። @Freshmerejaet @Freshmerejaet
ከጥርስ ቡርሽ እስከ ማንችስተር ሲቲ! የያቡ አርትስ አስደናቂ ድል በጥርስ ቡርሽ ታዋቂ ተጫዋቾችን በመሳል የሚታወቀው ኢትዮጵያዊው ወጣት ባለጥበብ ያብ አርትስ (Yabu Arts)፣ የማንችስተር ሲቲውን ክንፍ ጀርሚ ዶኩን በልዩ ጥበብ ስሎ አቅርቧል። ከ60 ሚሊዮን በላይ ተከታይ ያለው የማንችስተር ሲቲ ኦፊሴላዊ የፌስቡክ ገፅም በስራው በመደመም ቪዲዮውን በገፁ ላይ አጋርቶታል። ይህ ድንቅ ስራ የአለም አቀፍ እውቅናን ያተረፈ ሲሆን ለኢትዮጵያዊው ወጣት ትልቅ ኩራት ሆኗል። @Freshmerejaet @Freshmerejaet