tgindex
ትምህርተ ሃይማኖት ርትዕት

ትምህርተ ሃይማኖት ርትዕት

Статистика

በወንጌል ኮነ ህይወትነ ህይወታችን በወንጌል ሆነ ቅ / ያሬድ ማንኛውም ሐሳብ አስተያየት ካለዎት @bruk1993 ላይ መስጠት ይችላሉ

Последний пост
11 авг.
Последнее чтение
15 авг.
Постов за неделю
1
Всего постов
20
Тип
открытый
Язык
am
Категория
Книги (по похожим)
В каталоге с
13 авг.
Подписчики
1 770
−1 за 2 дн.
Сутки
0
0,00%
Неделя
 
Месяц
 
Просмотров на пост
591
20 постов
Вовлечённость
33,4%
к подписчикам
Постов в день
0,1
всего 20
Упоминаний
0
каналов
Охват размещения
оценка
1/24сутки в ленте
157
1/48двое суток
179
1/72трое суток
194

Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.

Посты

  • видео или голосовое, без подписи

  • https://youtu.be/tBCqPGxgWOs?si=rHG_ygCOd2Uhcuh7

  • https://youtu.be/tBCqPGxgWOs?si=rHG_ygCOd2Uhcuh7

  • https://youtu.be/ro7NOwG37CY?si=B4EdpNhmYAgZ_EBq

  • https://youtu.be/ZXQYgypJyjs?si=hrVo-LUf7iq_e_d9

  • https://youtu.be/tbHCGPc_svU?si=6JkgJ_1vnFxUdt3e

  • https://youtu.be/ts1QAHeRFZU?si=9ly0aCb2lIEb8MQV

  • https://youtu.be/UHD34vVgXis?si=XtX9dPFBr5PxVa-K

  • መዝሙር ዘሰንበት መዝ በ፫ ዓርገ እግዚአብሔር ንባቡና ትርጓሜው ዓርገ እግዚአብሔር በቃለ ቀርን በይባቤ ዓርገ ወበቃለ ቀርን ወነበረ በየማነ አቡሁ፡ እግዚአብሔር በእልልታ፥ በመለከት ድምፅ ዐረገ። (መዝ 47፥5) "በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ።" (ማር 16፥19) መዝሙረ ዳዊትን የተረጓጎሙ መተርጉማን ጌታችን እግዚአብሔር ከሰባ ዘመን በኋላ በዘሩባቤል አድሮ ትሩፋንን ይዞ ነጋሪቱን እያስመታ መለከት እያስነፋ ከባቢሎን ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ። የዘሩባቤል መንግሥት የጌታ ፈቃድ ስለሆነ የዘሩባቤልን ለጌታ ሰጥቶ ዓርገ አለ። አንድም በይባቤ መላእክት በክብር በቅዳሴ በብርሃን በሥልጣን ዓረገ። ብለው ተርጉመዋል። የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ዕርገት የባሕርይ አምላክ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ ከተነሣ በኋላ ለሐዋርያት ትምህርተ ኅቡአትን መጽሐፈ ኪዳንን እያስተማረቸው ለዓርባ ቀናት በምድር ላይ ቆየ። በጉባዔ ታይቶ ያስተማረቸው ግን ሦስት ቀን ነው። የትንሣኤ፣ የአግብኦተ ግብር፣ በጥብርያዶስ በዓርበኛው ቀን ወደ ሰማይ ዓረገ ያረገበት ቦታ በቢታንያ አጠገብ የሚገኘው ደብረ ዘይት የሚባለው ተራራ ነው። ከአራቱም ወንጌላውያን የኢየሱስ ክርስቶስን የዕርገቱን ታሪክ የመዘገቡት ቅዱስ ማርቆስ እና ቅዱስ ሉቃስ ናቸው። ማር 16፥19 ሉቃ 24፥50 የእግዚአብሔር ቀኝ የተባለው ኃይሉ ሥልጣኑና የባሕርይ ክብሩ ነው። በቀኝ መቀመጥም በኃይል በሥልጣን በክብር መተካከልን እና የባሕርይ አምላክነትን ያሳያል። የጌታም ዕርገት ክርስቲያኖች በሰማያት ሥፍራ ከእርሱ ጋር አብረው እንዲቀመጡ ያረጋግጣል። ቆላ 3፥11 ኤፌ 2፥6 ዓርገ በስብሐት ውስተ ሰማያት ተኮነኑ ሎቱ መላእክት ኩሉ ኃይል ወኩሉ ፍጥረት፡ በክብር ወደ ሰማያት ዐረገ፤ መላእክት፣ ሥልጣናት፣ ኃይላትና ፍጥረታት ሁሉ ለእርሱ ተገዙ፡ (1 ጴጥ 3፥22) የክርስቶስ ዕርገት የመለኮታዊ ሥልጣኑን መገለጥ ነው። ሰማያዊና ምድራዊ ፍጥረታት ሁሉ ለእርሱ ይገዛሉ። ዘምሩ ለአምላክነ ዘምሩ፡ ለፈጣሪያችን ምስጋና አቅርቡ። አንድም ፈጣሪያችንን ፈጽማችሁ አመስግኑ። ዘምሩ ለንጉሥነ ዘምሩ፡ ለንጉሣችን ለክርስቶስ ምስጋና አመስግኑ። (መዝ 47፥6) ይህ መዝሙር የጌታችንን ዕርገት፣ በአብ ቀኝ መቀመጡን፣ መላእክትና ፍጥረታት ሁሉ ለእርሱ መገዛታቸውን እና እርሱን በምስጋና ማክበር እንዳለብን ያስተምራል። (ዓራራ) ለዘዓርገ ውስተ ሰማያት ተኮነኑ ሎቱ መላእክት ኩሉ ኃይል ወኩሉ ፍጥረት፤ 1 ጴጥ 3፥22 እግዚእ ለሰንበት በይባቤ ዓርገ ወበቃለ ቀርን፤ ለአምላክነ ዘምሩ: መዝ 47፥5) ወደ ሰማያት ላረገ፤ መላእክት፣ ኃይላትና ፍጥረታት ሁሉ ለእርሱ ተገዙ። የሰንበት ጌታ በእልልታና በመለከት ድምፅ ዐረገ፤ ለአምላካችን ዘምሩ። ይህ ዓራራት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በክብር ወደ ሰማይ መውጣቱን፣ መላእክትና ፍጥረታት ሁሉ ለእርሱ መገዛታቸውን፣ እንዲሁም ምእመናን በምስጋና እና በደስታ ንጉሣቸውን እንዲያከብሩ የሚጠራ ነው። (እዝል) ዓርገ እግዚአብሔር ውስተ ማኅደሩ ግሩም ዓርገ እግዚአብሔር በይባቤ ዓርገ ወበቃለ ቀርን መዝ 47፥5 ዓርገ በስብሐት ምስለ መላእክት ሉቃ 24፥51 ንዑ ነሀሉ ኀበ አምላክነ ንዑ ነሀሉ ኀበ ንጉሥነ ዕብ 4፥16 ወናክብር ሰንበቶ በጽድቅ፡ ኢሳ 58፥13 ግሩም የሆነው እግዚአብሔር ወደ መኖሪያው (ወደ ሰማያዊ ክብሩ) ወጣ፤ በእልልታና በመለከት ድምፅ ወጣ፤ በክብር ከመላእክት ጋር ዐረገ፤ ኑ ወደ አምላካችን እንቅረብ፤ ኑ ወደ ንጉሣችን እንቅረብ፤ ሰንበቱንም በጽድቅ እናክብር፡ ሰንበትን ማክበር ማለት ቀኑን ብቻ መጠበቅ ሳይሆን በጽድቅ፣ በንጽሕና እና በአምልኮ ለእግዚአብሔር መኖር ማለት ነው። ይህ እዝል ክርስቶስ በእልልታና በመለከት ድምፅ ወደ ሰማይ ዐርጓል፤ መላእክት ተቀብለውታል፤ እኛም ወደ አምላካችን እንድንቀርብ፣ ንጉሣችንን እንድናመልክ እና ሰንበቱን በጽድቅ እንድናከብር ያስተምረናል። የዕርገት ክብር የምእመናን ተስፋ ነው፤ ራሱ ጌታ እንደተናገረው፦ "እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ ትሆኑ ዘንድ" (ዮሐንስ 14፥3) (ሰላም) ለዘዓርገ በስብሐት ውስተ ሰማያት ማር 16፥19 ተኮነኑ ሎቱ መላእክት ወይቤሎሙ ሰላም ለክሙ ዮሐ 20፥19 ኢይደንግጽክሙ ልብክሙ። ዮሐ 14፥1 በክብር ወደ ሰማያት ለዐረገው (ለክርስቶስ) መላእክት ተገዙለት፤ እርሱም፦ 'ሰላም ለእናንተ ይሁን፤ ሹመት ሽልማት ቀረብን ብላችሁ ልቡናችሁ አይሸበርባይሁ አላቸው። ይህ ሰላም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን አሸንፎ ከተነሣ በኋላ በክብር ወደ ሰማይ መውጣቱን ያሳያል። ወደ ሰማይ ሲያርግ መላእክት ለእርሱ ተገዙ፤ ይህም እርሱ የመላእክት ጌታ እና የሁሉ ንጉሥ መሆኑን ያመለክታል። (ዝማሬ) ወበዕርገቱ ለክርስቶስ ተጋብኡ በበይናቲሆሙ ወቆሙ በፍርሃት፡ ወወጽኡ ይትለአክዎ፡ ክርስቶስ በዐረገ ጊዜ ሐዋርያት በመካከላቸው ተሰብስበው በፍርሃት ቆሙ፤ ሲያርግም ይመለከቱት ነበር። (ሐዋ. 1፥9) ዓርገ ውስተ አርያም በስብሐት ወበይባቤ እንዘ ይኔጽርዎ ሰብእ ወመላእክት፡ ሰዎችና መላእክትም እየተመለከቱት በክብርና በምስጋና ወደ ላይ አረገ። (መዝ. 47፥5) ወተመነዩ ይርአዩ ትስብእቶ ለወልደ እግዚአብሔር (1 ጴጥ. 1፥12) እስመ መንክር ወዐቢይ ምሥጢር ውእቱ በፈቃዱ አስተርአየ ወሠምረ ይኔጽርዎ በሥጋ፡ የእግዚአብሔር ወልድ ሰው መሆኑን ለማየት ተመኙ፤ ምክንያቱም ይህ ድንቅና ታላቅ ምሥጢር ነውና በፈቃዱ በሥጋ ተገለጠ። መላእክት እንኳ የእግዚአብሔር ወልድ ሰው ሆኖ መገለጡን ለማየት ይመኙ ነበር። (1 ጴጥ. 1፥12) እግዚአብሔር ሰው ሆኖ መገለጡ፣ መሞቱ፣ መነሣቱና ማረጉ ታላቅ ምሥጢር ነው። (1 ጢሞ. 3፥16) ወሀበነ ሥጋሁ ኅብስተ ሕይወት ወደሞ ክቡረ ለሥርየተ ኃጢአት፡ ሥጋውን የሕይወት እንጀራ፣ ደሙንም ለኃጢአት ስርየት የከበረ ስጦታ አድርጎ ሰጠን። (ዮሐ. 6፥51) (ማቴ. 26፥28) ጽሑፍ በእንቲአሁ ተቀበለቶ ደመና እንዘ የዐርግ ወአኮ ዘጾረቶ አላ መጽአት ኀቤሁ በእንተ ዕበየ ግርማሁ፡ በዚያን ጊዜ ወደ ላይ ሲያርግ ደመና ተቀበለችው። ደመናይቱ እርሱን ተሸክማ ያሳረገችው አይደለችም፤ ነገር ግን ስለ ታላቅ ግርማው ወደ እርሱ መጥታ ተቀበለችው። እርሱ ግን በራሱ ፈቃድና በራሱ ኃይል ያረገ ነው። ወውእቱ ባሕቲቱ ዘዓርገ በፈቃዱ ወተቀበለቶ ደመና በውስተ መካና በከመ ተቀበልዎ ሊቃነ መላእክት ወተኮነኑ ሎቱ፡ ደመናይቱም በሰማያዊ ስፍራ ተቀበለችው፤ እንዲሁም ሊቃነ መላእክት (የመላእክት አለቆች) ተቀብለውት ለእርሱ ተገዙለት። ይህ ዝማሬ የጌታችን የዕርገት ክብርን ይገልጻል። ክርስቶስ በራሱ ሥልጣን ወደ ሰማይ አረገ፤ መላእክትና ሰዎችም የሥጋ መውሰዱንና የማዳን ሥራውን አድንቀው ተመለከቱ። ደመና መቀበሏ የመለኮታዊ ክብሩ ምልክት ነው፤ ቅዱስ ቁርባንም ለሕይወትና ለኃጢአት ስርየት የሰጠን ታላቅ ጸጋ መሆኑን ያስተምራል። ማሳሰቢያ ክቡራን ቤተሰቦቼ ሁልጊዜ ዓረብ ከምሽቱ 1:20 እሑድ የሚዘምሩት መዝሙር፣ ዓራራት፣ እዝል፣ ሰላም፣ ዝማሬ ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር በማገናኘት ስለሚብራሩ በፊስቡክ፣ በቴሌግራም ፣ በቲክቶክ እንድትከታተሉ በእግዚአብሔር ስም አሳስባለው። ፔጁን #በቀናነት ሰብስክራይብ #Like Follow Share በማድረግ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርት ያግኙ !!

  • https://youtu.be/hZ7-EnciZ-E?si=fpc1thOmhkgopoJK

  • https://youtu.be/o-nsB1OiYWc?si=EqJfT96gFzDYcJTv

  • https://youtu.be/Suvf8VomzLI?si=JSZXy6JYPXwxnMZx

  • https://youtu.be/3amNlpBKHUY?si=odquY5-ZGtISy69e

  • https://youtu.be/PcRfDj5ijCo?si=JYxjoyzUmFRyHPFb

  • https://youtu.be/VIlDgICF5Nw?si=MfOHoa-K0aqgC78E

  • https://youtu.be/B6Cf1a948Fs?si=gvu3y4Z4baabj7Op

  • https://youtu.be/Z7Z7StIWtJM?si=EfTHRdOV5dyU0Ghw

  • https://youtu.be/U4NLrzJ3mtE?si=0FKRB9MNQUy3BQTX

  • በ፭ር ወበእሑድ ሰንበት ጌሰት ማርያም መግደላዊት በፅባሕ ኀበ መቃብር እንዘ ዓዲ ( እንዘ ዓዲሁ) ጽልመት ወረከበት እብነ እቱተ እም አፈ መቃብር ወበጽሐት ኀበ ስምዖን ጴጥሮስ በኀበ ካልዕ ዘያፈቅሮ ኢየሱስ ወትቤሎሙ ነስእዎ  ለእግዚእየ እምውስተ መቃብር ወኢየአምር ኀበ ወሰድዎ እንዘ ይረውፁ ፪ሆሙ ኅቡረ በደሮ ለጴጥሮስ ዝኩ ካልዕ ረድእ ዘያፈቅሮ ክርስቶስ #በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበ መልዕክታት ወንጌልና ምስባክ፡፡ ዲ/ን 2ቆሮ5÷11-ፍ.ም ን/ዲ 2ጴጥ 3÷10- ፍ.ም ን/ካ ግብ፡ሐዋ 21÷31- ፍ.ም ፡#የዕለቱ_ምስባክ      መዝ 16÷5 ይእዜ እትነሣእ ይቤ እግዚአብሔር እሬሲ መድኃኒተ ወአግህድ ቦቱ ቃለ እግዚአብሔር ቃል ንጹሕተ ትርጉም፦ ዛሬ እነሣለሁ ይላል እግዚአብሔር መድኃኒትን አደርጋለሁ በእርሱም እገለጣለሁ የእግዚአብሔር ቃል ንጹሕ ቃል ነው #የዕለቱ ወንጌል፦     ሉቃ 24፥13-33 ቅዳሴ፦   ዘዲዮስቆሮስ ለወዳጅዎ ያጋሩ በTelegram 👉 @meskal በ YouTube 👉 ሊቃናተ ነድ Liqanat በ Instagram 👉 liqanatened

  • видео или голосовое, без подписи

ትምህርተ ሃይማኖት ርትዕት — tgindex