- Последний пост
- 15 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 3
- Всего постов
- 23
- Тип
- открытый
- Язык
- und
- Категория
- Книги (по похожим)
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 783
- 1/48двое суток
- 897
- 1/72трое суток
- 967
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
ሶስቱ የ 'መ' ህጎች ማርሽ ቀያሪ 👉መረዳት፣ 👉መተግበር፣ 👉መለወጥ መልካም ቅዳሜ !❤❤❤❤
👉ያለፈውን እርሳ 👉አሁንን በርታ 👉መጪውን ተጠንቀቅ !! ከሀሳበ ሰውነት ( red line ) ❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤
አንደኛ፦ ትችትን ችላ በል። ሁለተኛ፦ የራስህን መንገድ ምረጥ። ሶስተኛ፦ ብቻህን መሆንን ተለማመድ።" መልካም ውሎ !❤ ሀሳቦቼን አለመውደድ ይቻላል 👍 ወይም 👎
ጨለማው ምንም ያህል ቢበረታም፣ የማይነጋ ሌሊት እና የማያልፍ ችግር በምድር ላይ የለም። እንባና ሀዘን መንገድ ላይ ቢገጥሙንም፣ እግር ግን ወደፊት ከመራመድና ከመታገል በፍጹም አይቆምም። ችግር አእምሮን ሊያደክም ይችላል፤ የእምነትና የተስፋን ጥንካሬ ግን ሙሉ በሙሉ ሊያጠፋው አይችልም። አይዟችሁ ጓደኞቼ በርቱ እንበርታ ከሀሳበ ሰውነት ( red line ) መልካም አዳር ❤❤❤❤❤
ገንዘብ ማለት የነፃነትና የክብር በሮችን የሚከፍት ታማኝ ቁልፍ ነው። 👉 ገንዘብ ደስታን በራሱ ባይገዛም፣ በድህነት ምክንያት ከሚመጣ መከራና ውርደት ግን ይታደግሃል። ገንዘብ የሌለው ሰው ሕልሙን ለማሳካት ሲታገል፣ ገንዘብ ያለው ግን ሕልሙን የመኖር እድል ያገኛል። ገንዘብ ጥሩ ጌታ ባይሆንም፣ ለሕይወት አስፈላጊ የሆኑ መሠረታዊ ፍላጎቶችን የሚያሟላ ታላቅ አገልጋይ ነው። በመጨረሻም፣ ገንዘብን መውደድ ስህተት ቢሆንም፣ አስፈላጊነቱን መካድ ግን ለከፋ ችግር መዳረግ ነው። እውነቱ ይሄ ነው !! ከሀሳበ ሰውነት ( red line )
ስስታምነት ማለት የያዙትን ላለማጣት በመፍራት፣ የሚኖሩትን ሕይወት አጥቶ መኖር ማለት ነው። ስስታም ሰው የገንዘቡ ጌታ ነኝ ብሎ ያስብ፣ እውነቱ ግን ለቆጠረው ገንዘብ ባሪያ ነው። የማይሰጥ እጅ፣ አዲስ በረከትን ለመቀበልም ዝግ ነው ። ስስታም ሰው ሀብቱን በጥንቃቄ ይጠብቃል፤ ነፍሱን ግን በቁሙ አስሮ ያጠፋታል።ስስታም ማለት ብዙ ያለው ባለሀብት ሳይሆን፣ የገዛ ሀብቱን ለመጠቀም የሚፈራ ምስኪን ደሀ ነው። ከሀሳበ ሰውነት ( red line )
ወሲባዊ ቅንዝራምነት ማለት አእምሮን በስሜት እሳት አቃጥሎ፣ ነፍስን የሥጋ ባሪያ የሚያደርግ ሰይጣን ነው ። ትልቁ አሳዛኝ እውነት፡ ከልክ ያለፈ የሥጋ ፍላጎትን ለማርካት በሮጥክ ቁጥር፣ ጥሙ እየባሰ እንጂ እየቆመ አለመሄዱ ነው። ቅንዝራም ሰው ፍቅርን በፍላጎት፣ ክብርን ደግሞ በጊዜያዊ እርካታ ለውጦ የሚነግድ የተታለለ ፍጡር ነው። የሥጋ ስሜትን ለመቆጣጠር ያልቻለ ሰው፣ የገዛ አካሉ እስር ቤት ውስጥ የሚኖር ምስኪን እስረኛ ነው። በመጨረሻም፣ ቅንዝራምነት የፍቅር መግለጫ ሳይሆን፣ የውስጥ ባዶነትን በጊዜያዊ ስሜት ለመሸፈን የሚደረግ ከንቱ ጥረት ነው። ከሀሳበ ሰውነት ( red line )❤❤ መልካም ቅዳሜ
ሀገርን አለመውደድ ማለት ሞኝ ሲያብድ እንደማለት ነው ።ትልቁ አሳዛኝ እውነት፡ እናቱን እንደጠላ ልጅ፣ ሀገሩን የሚጠላ ሰው በሄደበት ሁሉ እንግዳ እና ባዕድ ሆኖ መቅረቱ ነው።የገዛ ሀገሩን የሚንቅ ሰው፣ የሌሎችን ሀገር ቢመኝም በነሱ ዘንድ ዘላቂ ክብር አያገኝም።ሀገርን መጥላት የራስን ማንነት ማጥፋት ነው፤ የራስህን ቤት አፍርሰህ በሰው ቤት ጥላ ስር መጠጋት አይቻልም። በመጨረሻም፣ ሀገሩን የማይወድ ሰው ከፍታ ላይ ቢደርስም፣ ስር የሌለውና በትንሽ ንፋስ የሚወድቅ ምስኪን ዛፍ ነው። ከሀሳበ ሰውነት ( red line ) መልካም የስራ ቀን❤❤❤❤
ሆዳም ሰው ማለት ሰውነቱን ለመመገብ በሚያደርገው እብደት ውስጥ፣ ነፍሱን በምግብ ሳህን ውስጥ አጥልቆ የሚገድል ሞኝ ሰው ማለት ነው። ❤ ትልቁ አሳዛኝ እውነት፡ ከልክ በላይ የበላኸው ምግብ ሁሉ፣ በመጨረሻ አንተን መልሶ መብላት መጀመሩ ነው።የሆዳም ሰው አምላኩ ከርሱ ነው፤ መቃብሩንም የሚቆፍረው በገዛ ጥርሶቹ ነው።ያለ ልክ መመገብ ሰውነትን ያወፍራል፤ አእምሮን ግን ባዶውን ያስቀራል።በመጨረሻም፣ ሆዳም ማለት በልቶ የጠገበ ሰው ሳይሆን፣ የሆዱ ባሪያ ሆኖ የቀረ ምስኪን ፍጡር ነው። ከሀሳበ ሰውነት ( red line ) መልካም አዳር !!!!❤❤❤❤❤
የሌሎችን ሰወች ስቃይ እንደ መዝናኛ ማየት የሰውን ልጅነት ገድሎ የአውሬነትን መልክ መልበስ ነው፤ የሌላውን እንባ የሚያብስ እንጂ የሚያፈስ ፍጡር የሰውነት ክብር የለውም።በሰው መብትና ህመም ላይ የሚሳለቅ የስልጣን ወይም የጉልበት ባለጊዜ ጥማታም፣ ውሎ አድሮ የራሱን መቃብር ከክፉ ትዝታ ጋር ይቆፍራል።የሚደክሙ፣ የሚጥሩ፣ የሚለፉ ሰወችን ውርደትና መከራ እንደ ድል የሚቆጥር ልብ፣ ከሰው ዘር ተርታ ተሰልፎ ግን የሰብአዊነትን ትርጉም ፈጽሞ የማያውቅ ነግ በእኔ የሌለው የባከነ ፍጡር ነው ! ከሀሳበ ሰውነት ( red line )❤ መልካም ቀን
የህይወት ደስታ ጠፋብኝ ብሎ ማማረር በራስ እጅ በታጠረ የጨለማ ቤት ውስጥ ሆነው ፀሐይን ጠፋች እያሉ እንደማልቀስ ነው።ደስታን ከውጭ እቃዎችና ከሰዎች ፈገግታ ብቻ ስትጠብቅ፣ የራስህን የውስጥ ሰላም ገድለህ የሌሎች ሎሌ ትሆናለህ።የደስታን ትርጉም ሳያውቁ መኖር ከትንፋሽ ውጪ ምንም የሌለው አስከሬን መሆን ነው፤ ህይወትን በማማረር ማባከንም ትልቁ ኃጢአት እርሱ ነው። ከሀሳበ ሰውነት (red line) መልካም አዳር
የሶማሊላንድ ፕሬዚዳንት የኩላሊት ንቅለ ተከለ ህክምና በመላ ሀገሪቱ በነፃ እንዲከናወን መመርያ አውርደዋል ! ብራቦ ! እግዚአብሔር ሆይ ኢትዮጵያንም ተመልከታት እባክህ ! የመረጃ ምንጭ ዘ ሀበሻ
የሰውን ጥረትና ወዝ ዘርፎ መኖር ብልህነት ሳይሆን የውስጥ ድህነት ማሳያ ነው፤ ነጥቆ መብላት መቼም ቢሆን ክብርን አያጎናጽፍም።በድብቅ የተወሰደ ሀብት ጊዜያዊ እርካታን ይሰጥ ይሆናል፤ ውሎ አድሮ ግን ሰላምህን ነጥቆ በውርደት ማቅ ይሸፍንሀል።ለፍቶ ማግኘት ሲያቅት መዝረፍ ህሊናን በቁም መቅበር ነው።የሌሎችን ጥረት በጉልበት ወይም በብልጠት መውሰድ ትልቅ ድል ሳይሆን፣ የራስን አቅም አልባነትና ኋላቀርነት በግልጽ ማሳየት ነው። ከ ሀሳበ ሰውነት red line መልካም አዳር ❤❤❤❤❤
የፍቅር ረሃብ ከባዶነት የሚጀምር ቢሆንም፣ መጨረሻው ግን የራስን ማንነት አሳልፎ በመስጠት ርካሽነት ይደመደማል።በየመንገዱ ፍቅርን እየለመኑ መዞር ልብን አያረካም፤ ይባስ ብሎ የራስን ዋጋ አዋርዶ ለሌሎች መጫወቻ ያደርጋል።ማንም እንዲወድህ ስትል የምታሳየው ከመጠን ያለፈ ጥማት፣ እራስህን ሳትሆን የሌሎችን ምህረት እንድትለምን ያደርግሃል።የእውነተኛ ፍቅር እጦት መፍትሔው ማንኛውም ማዘናጊያ አይደለም፤ ራስን መውደድ ሲሳንህ የሚፈጠር የውስጥ ባዶነት ግን በምንም ሊሞላ አይችልም። ከሀሳበ ሰውነት ❤መልካም ቀን
በቁጥጥር ስር ያልዋለ ፍላጎት ዛሬን እንድትበላው ሲያደርግህ፣ ነገ ግን እርሱ ይበላሃል። የተራበ አፍን ማስታገስ በረከት ነው፤ የጥጋብን ጥማት ግን መቼም ቢሆን መሙላት አይቻልም። የዚህ ዓለም ትልቁ ውርደት፣ ከምግብ ማነስ ሳይሆን ከልክ ያለፈ ፍላጎት ተገዢ ሆኖ መገኘት ነው። ሆድ ሲሞላ አዕምሮ ባዶ ይቀራል፤ ማባሪያ የሌለው የጥጋብ ሩጫም ሰውነትን እንጂ ክብርን አያሳድግም። ከ ሀሳበ ሰውነት ( red line )
የወንድን ልጅ ማንነት የሚገነቡ ሶስት ነገሮች፦ 👉 ዲሲፕሊን፦ ያለ ሰው ቁጥጥር ራሱን መምራት። 👉 ቃሉን መጠበቅ፦ ከተናገረው በላይ በተግባር መገኘት። 👉 አለመበገር፦ ውድቀት ሲገጥመው እንደገና ተነስቶ መሞከር። ይህንን መርህ ለሚከተሉ ጓደኞችዎ ይላኩላቸው ከሀሳበ ሰውነት
ስለ ወንድ ልጅ ምስክርነት👉👉👉 👉👉👉👉👉👉👉👉👉 ❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤ ትከሻው የብዙዎችን ሐዘን ቢሸከምም፣ ለብቻው ሆኖ የሚፈሰው እንባው ከማንኛውም ውቅያኖስ በላይ ጥልቅ ነው።ፀጥታው ድክመት ሳይሆን፣ ቤተሰቡንና ዓለሙን ለማቆም በውስጡ የሚያካሂደው ጸጥ ያለ ጦርነት ነው።በውጭው አለም ጫና የተሰባበረ ቢመስልም፣ ፍቅሩንና ኃላፊነቱን በታማኝነት በመወጣት ከእያንዳንዱ ውድቀት በኋላ አዲስ ጀግና ሆኖ ይነሳል። ክብር ለወንድ ፆታ !!!!! ከ ሀሳበ ሰውነት
የጠዋት ፀሐይ ብርሃን መስኮትህን ጥሶ ሲገባ፣ ትላንት ያሳሰበህ ነገር ሁሉ ትዝታ ብቻ ሆኖ ታገኘዋለህ።ዛሬ አዲስ ዕድል፣ አዲስ ጅማሬ እና ከየትም የሚመጣ ያልተጠበቀ ውብ ምዕራፍ ነው።ፈገግታህን ለአለም አትንፈጋት፤ ምክንያቱም ዛሬ ቀንህ ነው። ከሀሳበ ሰውነት
ሰይጣን ነፃ ስጦታ የለውም። ላደረገልህ ነገር ሁሉ በመጨረሻም አስከፊውን እና የምታዝንበትን ዋጋ ያስከፍልሀል!!
ወዳጄ ገንዘብ የለህም ማለት ድምጽ የለህም ማለት ነው ..... እንደ ምንም ብለህ ገንዘብ ያዝ ! አመጣጡ ላይ ብቻ ጥንቃቄ አድርግ !!! የሰው እንዳትነካ !!!