Abay Forum
Статистика- Последний пост
- 15 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 11
- Всего постов
- 25
- Тип
- открытый
- Язык
- und
- Категория
- Новости и СМИ (по похожим)
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 172
- 1/48двое суток
- 197
- 1/72трое суток
- 212
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
видео или голосовое, без подписи
https://www.youtube.com/live/I6JhoXCy9BE?si=KKQENcrR5DI5Vfyd
https://www.youtube.com/live/n68u3t5jyl4?si=9i-rSx5M2No6Zecj
Amhara Satellite Television (AmharaSAT Tv) support options; You can find all support and membership options by checking Amharasat.org website. የአማራሳት ድህረ፟ገፅን በመጎብኘት አማራሳትን መደገፍ እና ቋሚ አባል መሆን የሚችሉባቸውን አማራጮች ያገኛሉ! 1. amharasat.org/support-us/ 2. Zelle, CashApp, PayPal: 720-309-3725 3. PayPal Link: paypal.com/donate/?hosted… 4. Donate by Card: amharasat.org/donate/ 5. GoFundMe:gofund.me/4402fb5d8 6. Membership: amharasat.org/subscribe/
https://youtu.be/vNAl8WGpYrc
♦ ማስታወሻ ደብተራችሁን አውጡ! – እነ ጸጋዬ አራርሳ ያመለጣቸው የ16ኛው ክፍለ ዘመን የታሪክ ትምህርት 😁 (በይድነቃቸው ከበደ) 1. የኦሮሞ ህዝብ መነሻና ጥንታዊ መኖሪያ ፤ ከ16ኛው ክፍለ ዘመን ታላቅ የህዝብ እንቅስቃሴና ፍልሰት በፊት፣ የኦሮሞ ህዝብ ዋና መገኛ ግዛት በደቡባዊ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ቦታዎች እና በሰሜን ኬንያ አዋሳኝ ስምጥ ሸለቆ አካባቢዎች ነበረ። የመሃል ማዕከሉ "ማዳ ወላቡ" (በአሁኑ የባሌና ቦረና አዋሳኝ) በመባል ይታወቃል። የጎሳ አደረጃጀት ፤ ቦረና (በደቡብና ደቡብ ምዕራብ) እና ባሬንቱ (በደቡብ ምስራቅ) የኑሮ ዘይቤ ፤ በዋነኝነት ከብት አርቢ የነበረና ህይወቱ ከግጦሽ መሬትና ከዝናብ ዑደት ጋር የተቆራኘ ነበረ። 2. የ16ኛው ክፍለ ዘመን የኦሮሞ መስፋፋት (Oromo Expansion / Movement) ከ1520ዎቹ ጀምሮ በክርስቲያኑ የኢትዮጵያ መንግሥት እና በአዳል ሱልጣኔት (በአህመድ ግራኝ) መካከል በነበረው አውዳሚ ጦርነት ሳቢያ የተፈጠረውን የኃይል ክፍተት በመጠቀም፣ የኦሮሞ ህዝብ እንቅስቃሴ በሶስት ዋና ዋና አቅጣጫዎች ተካሄዷል ። ሀ. ወደ መካከለኛውና ምዕራብ ኢትዮጵያ የመጫ እና የቱለማ ቅርንጫፎች ወደ ሸዋ፣ ወለጋ፣ ኢሉባቦር፣ ጂማ እና ከፋ አካባቢዎች። ለ. ወደ ምስራቅ ኢትዮጵ ፤ የባሬንቱ ወገኖች (ኢቱ እና ሀምባና) ወደ ሐረርጌ እና አርሲ። ሐ. ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ ፤ የወሎ እና የጁ ኦሮሞዎች መካከለኛው ሸዋን አቋርጠው እስከ ወሎ፣ ደቡብ ትግራይ እና ጎንደር አዋሳኝ። 3.በOromo Expansion / Movement የማህበራዊና ስነ-ህዝብ ለውጦች (የጠፉና የተዋሃዱ ብሔሮች ፤ የማስፋፋት ሂደቱ በየ8 ዓመቱ በሚካሄደው የገዳ "ሉባ" ዘመቻ እንዲሁም በባህላዊ ውህደት ስርዓቶች (ሞጋሳ እና ጉዲፈቻ) አማካኝነት ተከናወነ። በዚህ ሳቢያ የሚከተሉት ጥንታዊ ህዝቦችና መንግሥታት ታሪካዊ ህልውናቸውን አጥተዋል ወይም በማህበረሰቡ ውስጥ ቀልጠዋል፦ ሀ. ጋፋት ፤ በአባይ ወንዝ ዙሪያና በምስራቅ ጎጃም/ወለጋ ይኖሩ የነበሩ ሲሆን፣ በሂደት ቋንቋቸውና ማንነታቸው ጠፍቷል ። ለ. የዳሞት መንግሥት ፤ ህዝቡ ወደ ሰሜን (ጎጃም) ለመሰደድ ተገዷል፤ የቀረውም በኦሮሞ ማንነት ውስጥ ቀልጧል ። ሐ. ፈጠጋር እና ጋንጅ ፤ በመካከለኛውና ምስራቅ ኢትዮጵያ (ሸዋና አርሲ) የነበሩ ህዝቦች ሲሆኑ፣ በሞጋሳ ስርዓት ተዋህደዋል። መ. የእንጅናርያ መንግሥት፤ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የነበረ ባለጸጋ የኦሞቲክ/ሲዳማ መንግሥት ሲሆን፣ በሊሙ ኦሮሞዎች እንቅስቃሴ ፈርሷል። ሠ. ሐዲያ እና ሲዳማ ፤ ሰፊ ግዛታቸውን ያጡ ሲሆን፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝባቸው በሞጋሳ ስርዓት ተዋህዷል ። 4. ከ16ኛው ክፍለ ዘመን በፊት የአዲስ አበባ (በረራ) ገጽታ ፦ አሁን አዲስ አበባ የምትባለው ስፍራ ከ16ኛው ክፍለ ዘመን በፊት በታሪክ ማህደሮች "በረራ" በሚል ስም የምትታወቅ የኢትዮጵያ ነገሥታት (የሰሎሞናዊው ሥርወ-መንግሥት) ዋና ከተማና የንግድ ማዕከል ነበረች። እንደ አፄ ዳዊት፣ አፄ ይስሐቅ እና አፄ ዘርአ ያዕቆብ ያሉ ነገሥታት ቤተ-መንግሥት የሰሩበት ስፍራ ነበረች። በጊዜው በአካባቢው ይኖሩ የነበሩት ነባር ህዝቦች፦ የአማራ ህዝብ ፤ የመካከለኛው ሸዋ የክርስቲያኑ መንግሥት እምብርት በመሆኑ በስፋት ይኖርበት ነበር። የጋፋት፣ የጉራጌ እና የአገው ህዝቦች በአሁኑ አዲስ አበባ እና ዙሪያዋ ባሉ የሸዋ ክፍሎች ከጥንት ጀምሮ ይኖሩ የነበሩ ሴማዊና ኩሻዊ ቋንቋ ተናጋሪዎች ነበሩ። ማጠቃለያ ! የታሪክ ድርሳናት እንደሚያስረዱት፣ ከ16ኛው ክፍለ ዘመን የታላቁ ህዝቦች እንቅስቃሴ በፊት አሁን አዲስ አበባ የምትባለው "በረራ" አማራ፣ ጋፋት፣ ጉራጌ እና አገው ህዝቦች ይኖሩባት የነበረች ታሪካዊ ቦታ እንጂ የኦሮሞ ህዝብ ነባር መኖሪያ አልነበረችም። እርግጥ ነው፣ የወቅቱ የፖለቲካ ተንታኞች ይህን የታሪክ ሂደት አይፈልጉትም ፤ አሁን ባለው ህገ-መንግስት መመራት አለብን የሚል ሙግት ያቀርባሉ፤ ሆኖም የታሪክ እውነታውን መካድ ግን ፈጽሞ አይቻልም ፤ ለዘላቂ መፍትሄ መሰረት አይሆንም። የታሪክ ድርሳናት ማጣቀሻዎች (Sources) • Prof. Richard Pankhurst – "The Ethiopian Borderlands" (1997) • Prof. Taddesse Tamrat – "Church and State in Ethiopia (1270-1527)" • Abba Bahrey – "Zenahu Galla" (1593) • Prof. Mohammed Hassen – "The Oromo of Ethiopia: A History 1570-1860" • Ulrich Braukämper – "Islamic History and Culture in Southern Ethiopia" • Prof. Getachew Haile –"የአባ ባሕርይ ድርሳናት" በይድነቃቸው ከበደ
https://www.youtube.com/live/Tfx1pYWp6uM?si=64nOfcHzLJqdjVqd
አማራሳት ቴቪ
ውድ አድማጭ ተመልካቾቻችን ወደ እናንተ ስንደርስበት የነበረው Abc breakdown የዩትዩብ ቻናላችን ስለተዘጋ፣ የዛሬው እለታዊው የትኩረት 30 ዝግጅታችንን ለመከታተል ከታች ያለውን ቻናል ሰብስክራይብ በማድረግ ይጠብቁን። 👇 https://youtube.com/@astvnews1?si=s1G45dsPDZetB64J
https://www.youtube.com/live/EPydKMl3qss?si=UxRg1PJBaLTijo9Z
https://youtu.be/0OR9IOkAjXw
https://youtube.com/live/i5cvCSYLJRg?feature=share
https://youtube.com/live/VhlWKGTHgSI?feature=share
ቅን አገራዊና አማራዊ መሻት ያሸንፋል‼ በአማራው ትግል 'ወዲያ ወዲህ' ውስጥ፡ አይሆኑትን የሆነው፣ የማይባልን ያለው፣ ነገን የዘነጋው የትየለሌ ነው። 'አፍልቶም' ፡ 'ፈልቶበትም' ፡ ጥጉን የያዘው በራዥና አቆርቋዥ ቀላል አይደለም። ➻ ከግንባር-ድርጅት በዜግነት ጎራ ተሰልፎ ያንገላታን ባለገንዘብ፣ ባለሚድያ፣ ባለወታደር ወዘተ ቀላል አልነበረም። ጥጉን ያዘ !! ➻ ባለኃይማኖት፡ የ"እምነት ወታደር" ዘማች-ሠራጊን ያሕል ከእኔ በላይ ባይ አልነበረም !! ጥጉን ያዘ !! ➻ የፋኖ የውጭ ወኪል፣ ገንዘብ ሰብሳቢ፣ መግለጫ ፃሐፊን ያሕል አላዋቂም ዳናው ጠፍቷል። ➻ በአማራ ስም የሚምል፣ ራሱን የትግሉ ፈራጅና ቀያሽ፣ አልፎም በስሙ የሚሠራለትን የተልዕኮ ፋኖ ለማደራጀት ሌት ተቀን የደከመና መድክሙን ያልተወ፣ የአማራን ተቋማትና መሪዎች ሁሉ በማብጠልጠል 'ከእኔ ወዲያ' የሚል ከንቱ ስብስብ ሁሉ ዛሬ ወደተራ የስድብ መንጋነት ተቀይሯል!! ➻ ራሱን የልዩ አማራዊ መንደር ተቆርቋሪ ያደረገው፣ በዚያው ደግሞ የሆነ አማራዊ መንደርን ጠላት አድርጎ፡ ''ከአማራ ጠላቶች ሁሉ ይብስብኛል ፥ እነሱ ከሚመጡና ከሚመሩ ምድር ትሰንጠቅ'' የሚለው መንጋም ላንቃውን ከመሰንጠቅ አልቦዘነም!! ➻ እንዲህና እንዲያ ያሉ ብዙ ነበሩ!! ተሸንፈዋል፣ ጥግ ይዘዋል !! ➻ በየጊዜውና በየደረጃው ችግር ይገጥማል !! ነገም ይገጥማል!! ተፈጥሯዊ ነው። አሸናፊው ግን ሐቀኛ መስመር ነው!! ቅን አገራዊና አማራዊ ፍላጎትና በጎ ምኞት ነው !! ዋናው ጥቃት ከራስ ድክመት ይነሳል !! ውጫዊው ጠላት የውስጥ ድክመትን ይጠቀማል !! ምክንያቱም ፦ << ደካማነትም ፀብ ጫሪነት ነው >> !!
https://www.youtube.com/live/EP7BOFOWjzs?si=ansKEUDZraZWuaPB
https://www.youtube.com/live/gDrqJRBj3SY?si=xrZDFu3WpTXFF9uM
https://www.youtube.com/live/o4DtH_gz7dg?si=8lCd0erVoG_JMAYi
https://youtube.com/live/-acKGpkRM2c?feature=share
https://youtu.be/mPUvVQjQUmo
https://youtube.com/live/Y6SD0c3EngA?feature=share