- Последний пост
- 20 июл.
- Последнее чтение
- 13 авг.
- Постов за неделю
- 0
- Всего постов
- 20
- Тип
- открытый
- Язык
- und
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 11 075
- 1/48двое суток
- 12 691
- 1/72трое суток
- 13 688
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
እርር ድብን! Gubadhaa Du'aa! Cadho iyo ciil u gubada! U dhinta! ⛔⛔⛔⛔⛔⛔⛔⛔⛔⛔⛔⛔ አንዳንዱ "ተበደልኩ" እያለ የራሱ መብት እንዲከበር ሲጮኽ የሚውል፣ ሌላው ተነስቶ 'የእኔም ጥያቄዎች እነዚህ ናቸው' ማለት ሲጀምር ግን ለቅሶውን አቁሞ 'እንዴት እነዚህን ጥያቄዎች ትጠይቃላችሁ?' እያለ መራገምና መሳደብ ይጀምራል። ተከታዮቹን ስድብና እርግማን እንዲያዋጡ ያስተባብራል። የሚገርመው ደግሞ እርሱም እንደ አንተው የመብት ጠያቂ እንጂ ምላሽ ሰጪ አለመሆኑ ነው። ገና በመጠየቅህ ብቻ እንዲህ የሚበሳጭና የሚንጨረጨር አካል፣ ጥያቄዎችህ ምላሽ ቢያገኙ አልያም ራሱ የሥልጣን ወንበር ላይ ተቀምጦ ጥያቄዎችን መመለስ ያለባት የመንግስት አካል ቢሆን ምን ሊያደርግ እንደሚችል አስበው! ጥያቄህን በይፋ የማቅረብና የመናገር መብት እንኳ እንዳለህ እውቅና የማይሰጥ አካል፣ ብዙም ሳይቆይ "የሀገሪቱ ችግር በእኛ ትግል ነው የሚፈታው፣ ትግላችንን መደገፍ አለባችሁ" እያለ ሲወተውት ታገኘዋለህ። "ታጋይ ነኝ"፣"ነጻ አውጪ ነኝ"፣"የዲሞራሲያዊ ስርዓት ሃዋሪያ ነኝ"፣ "የእኩልነት ጠበቃ ነኝ" የሚል ሁሉ እንደሚለው አለመሆኑን እስካሁን ካላስተዋልክ በእርግጥ አንተ ገና ብዙ ይቀርኻል። "በቁጭታችሁ ሙቱ" ⛔⛔⛔⛔⛔⛔ قُلۡ مُوتُواْ بِغَيۡظِكُمۡۗ إِنَّ ٱللَّهَ عَلِيمُۢ بِذَاتِ ٱلصُّدُورِ — سورة آل عمران (3:119) "በቁጭታችሁ ሙቱ፤ አላህ ልቦች የቋጠሩትን ዐዋቂ ነውና» በላቸው፡፡"(ኣሊ-ኢምራን (3:119) Gubadhaa Du'aa! ⛔⛔⛔⛔⛔⛔ Tokko tokko "miidhameera" jedhee mirgi isaa garuu booyicha isaa dhiisee 'akkamitti gaaffilee kana gaafattu?' jedhee abaaruufi arrabsuu jalqaba. Hordoftoota isaas arrabaa fi abaarsa akka gumaachan gurmeessa. Kan nama dhibu immoo isanis akka keetti gaafataa mirgaa ti malee deebii kennaa miti. Gaaffii kee dhiyeessuu keetiin qofa akkas kan aaruu fi boba'u, gaaffileen kee deebii yoo argatan ykn inni mataan isaa teessuma aangoo irra taa'ee qaama mootummaa gaaffilee deebisuu qabu utuu ta'ee maal gochuu akka danda'u mee tilmaami! Gaaffii kee ifatti dhiyeessuu fi dubbachuuf mirga akka qabdu illee beekamtii kan hin kennine, dhiyootti "rakkoon biyyaa qabsoo keenyaan furama, qabsoo keenya deggeruu qabdu" jedhee yommuu lallabu isa argita. "Qabsaawaadha", "Birmaduu baasaadha", "Ergamaa sirna dimookraasiiti", "Abukaatoo qixxummaati" kan jedhu hundi akka waan jedhuu dhiisuu isaa hanga ammaatti yoo hin hubatin, dhugumatti ati ammas baay'eetu si hafa. "Dallansuu keessaniin du’aa" ⛔⛔⛔⛔⛔⛔⛔⛔⛔⛔ قُلۡ مُوتُواْ بِغَيۡظِكُمۡۗ إِنَّ ٱللَّهَ عَلِيمُۢ بِذَاتِ ٱلصُّدُورِ — سورة آل عمران (3:119) "Dallansuu(gaabbi) keessaniin du’aa" jedhi, Dhugumatti Rabbiin beekaa waan qoma keessa jiruuti."(Qur'aana Suuraa Aali Imraan 3:119) Cadho iyo ciil u gubada! U dhinta! 🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥 Mid ayaa maalinta oo dhan taagani "Haqaygii ayaa la duudsiyay" oo u qaylinaya in xuquuqdiisa loo tixgeliyo. Balse markay kuwo kale kacaan oo yidhaahdaan "Anaguna kuwasaynu leenahay", wuxuu isla markiiba joojiyaa baroorashadii, wuxuuna bilaabaa cay iyo habaar isagoo leh "Sidaad ugu dhiirrateen inaad arrimahani soo raised-garaysaan?". Xitaa taageerayaashiisa wuxuu u habaubeeyaa inay aflagaado iyo qabyaalad cirka u ekaadaan! Ugu yaabka badani waa inuu isaguba sidada oo kale yahay xaq-doon kaliya, oo aynan ahayn kii go'aanka lahaa. Qof hadal kaliya oo aad tiddid ku cawilaya oo carro la gubtay, qiyaas waxa uu samayn doono haddii codsigaaga la meel-mariyo ama uu isagu berto kursiga maamulka ee go'aanka lehi fadhiysto! Qof aan xitaa ku tixgelinayn inaad si muuqata codkaaga u dhiibatid, ayaad dhoor maalmood ka dib ka helaysaa isagoo kugu laha "Dhibaatada dalka ka jirta waxay ku xallismaysaa haljankayaga, waa inaad na taageertaan." Haddii aad ilaa maanta fahmi weyday in qof kasta oo yidhaahda "Waxaan ahay halgame", "Waxaan ahay xoreeye", "Waxaan u taaganahay dimuqraadiyadda" ama "Waxaan ahay u doodaha sinnaanta" uusan ahayn sida uu sheeganayo... Runtii wax badan ayaa wali kugu dhiman. Cadho iyo ciil u gubada! U dhinta! ⛔⛔⛔⛔⛔⛔⛔⛔⛔⛔⛔⛔ قُلۡ مُوتُواْ بِغَيۡظِكُمۡۗ إِنَّ ٱللَّهَ عَلِيمُۢ بِذَاتِ ٱلصُّدُورِ — سورة آل عمران (3:119) "Dheh: U dhinta ciilkiinna. Hubaal, Alle waa Og yahay waxa ku jira laabaha (dadka)." (Aali-Imraan 3:119)
በነፍስ እርካታ የታዘብኩት የ«ኑር ኢስላሚክ ሴንተር» ድንቅ ታሪክ 🔴🥰🔴🥰🔴🥰🔴🥰🔴🥰 በለውጥ እና በዕውቀት ጎዳና ላይ ያሉ ወጣቶችን መጎብኘት ለነፍስ ትልቅ እርካታን ይሰጣል። ትናንት በነበረኝ ፕሮግራም፣ ከአስራ አምስት ዓመታት በፊት በታላቅ እልህና ተስፋ የተመሰረተውንና ዛሬ ላይ ፍሬያማ ጉዞ እያደረገ የሚገኘውን «ኑር ኢስላሚክ ሴንተር» የመጎብኘት ዕድል ነበረኝ። የዚህን ተቋም አመሰራረትና አሁን የደረሰበትን ደረጃ ስመለከት አላህ (ሱ.ወ) በቅን ልቦና ለሚነሱ ወጣቶች የሚያደርገውን እገዛ በአካል የተመለከትኩበት አጋጣሚ ሆኖልኛል። ታሪኩ እንዲህ ነው፦ የዛሬ 15 ዓመት ይህ ተቋም ሲመሰረት፣ መስራቾቹ አብዛኛዎቹ የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ (የሀይስኩል) እና የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የነበሩ ወጣቶች ነበሩ። በወቅቱ የነበረውን ማህበራዊና ሃይማኖታዊ ክፍተት ለመሙላት፣ ልክ እንደ መጀመሪያው የእስልምና የዕውቀት ማዕከል «ዳሩል አርቀም» በጠባብ 3 በ 3 ክፍል ውስጥ ነበር ስራቸውን የጀመሩት። ዛሬ ግን ያ አነስተኛ ክፍል አድጎና ጎምርቶ በየዓመቱ ከ500 በላይ ህጻናትን (ወንዶችንም ሴቶችንም) ከጀማሪ የቁርኣን ንባብ አንስቶ ማስተማር የቻለ፣ በርካታ ሀፊዞችንና የዲን ተረካቢዎችን ያፈራ ታላቅ ተቋም ለመሆን በቅቷል። ልዩ የሚያደርገውና ለሁላችንም አርአያ የሚሆነው ትልቁ ነጥብ፦ ይበልጥ ልብ የሚነካውና የወጣቶቹን የፅናት ጥግ የሚያሳየው ትልቁ እውነታ፤ በወቅቱ መድረሳዋን ለመክፈት የነበረባቸውን የ600 ብር የቤት ኪራይ ለመክፈል የቻሉት፣ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹ ከሚከፈላቸው የ240 ብር ኮስት ሼሪንግ (ኪስ ገንዘብ) ላይ 100 ብር እየቀነሱ በማውጣት ነበር! ያኔ መቶ መቶ ብር እያዋጡ የዲን ችግኝ የተከሉ ወጣቶች፣ ዛሬ ላይ ለተቋሙ ግንባታ ሂደት ከሚስፈልገው ወጪ ውስጥ ወደ 9 ሚሊየን ብር የሚጠጋውን ገንዘብ ያዋጡት ራሳቸው መስራቾቹ መሆናቸው ነው! ይህ በብዙ ቦታዎች ላይ ያልተለመደ፣ ለዲን ያላቸውን ቁርጠኝነትና የባለቤትነት ስሜት የሚያሳይ ደማቅ ምሳሌ ነው። «ኑር ኢስላሚክ ሴንተር» ዝም ብሎ የሚንቀሳቀስ ሳይሆን፣ የራሱን ዘመናዊ ካሪኩለም ቀርጾና ነድፎ፣ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ባካተተ መልኩ እያስተማረ የሚገኝ ተቋም ነው። በዚህ ስልታዊ ስራውም ማህበረሰባችንንና ወጣቶቻችንን ከተለያዩ የባህልና የአክፍሮት ኃይላት ጥቃት እየታደገ ያለ ጋሻ ነው። እኔም በዛሬው ጉብኝቴ ይህንን ታላቅ እውነታ በተጨባጭ ታዝቤያለሁ። ስለዚህ ውድ ሙስሊም ወንድም እህቶቼ እነዚህ ወንድሞቻችን በትጋት እየሰሩት ያለውን ስራ በአካል ሄዶ መጎብኘት፣ ማበረታታትና ለጀመሩት ታላቅ ግንባታ የሚያስፈልጋቸውን ወጪ ሁሉ ደግፎ ማጠናቀቅ የሁላችንም የጋራ ኃላፊነት ነው። ስለሆነም ይህ መልዕክት የደረሳችሁ በሙሉ፦ 1. ወደ ተቋሙ በአካል በመሄድ ወጣቶቹንና ስራቸውን እንድትጎበኙ፣ 2. ለግንባታው ስኬት የሚሆነውን የጎግል ፎርም ( https://forms.gle/61kqCgUDYRLTG7iq6)በመሙላት እና የሚያስፈልገውን የገንዘብ፣ የቁሳቁስና የዕውቀት ድጋፍ ሁሉ በማድረግ ከጎናቸው እንድትቆሙ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ። የኑር ኢስላሚክ ሴንተር የባንክ ሂሳብ ቁጥሮች CBE:- 1000611003092 Awash 014171302912701 DASHEN:- 7930469710011 ABYSSINIA:- 150900816 HIJRA:- 1005200010001 ZEMZEM:- 0038218810301
без подписи
7. Tajaajila Faayinaansii Maamiltootaaf Addaan Bahe 🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 Dhiyeessii faayinaansii waggaa baajataa darbe birrii bilioona 7.2 ture irraa %133 guddisuun, waggaa baajataa kanaan Birrii bilioona 16.78 ol faayinaansii godheera. Kanneen keessaa: Mushaarakadhaan: Birrii bilioona 1.6 (%9.54) Mudaarabahdhaan: Birrii bilioona 1.33 (%7.93) Qardul Hasan (Liqii bifa gargaarsaan / Karaa bilisaa): Birrii miilioona 341.72 (%2.03)** dhiyeessee jira. 8. Baay'ina Dameewwanii 🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈 Baankichi waggaa baajataa kana keessatti dameewwan haaraa 41 banuun, baay'ina dameewwan isaa waligalaa 170 biraan gaheera. 9. Faayinaansii Dijitaalaa 🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵 Hojiiwwan xixiqqaa fi giddu-galeessaa keessatti kan hirmaataniif, akkasumas dubartootaa fi dargaggoota 3,871 ta'aniif wabii dandeettii dabalataa malee Birrii bilioona 1.5 Faayinaansii I-Muraabahaa dhiyeessuu danda'eera. 10. Baankii Dijitaalaa (Digital Banking) ❄❄❄❄❄❄❄ Baankichi waggaa baajataa kanaan baay'ina maamiltoota baankii dijitaalaa waligalaa miilioona 2.24 biraan gahuu dandeessiseera. Hojii sochiilee maallaqa dijitaalaan taasifame Birrii bilioona 41.72 (guddina %86), akkasumas baay'inni tajaajila daldalaa (transactions) 261,982 (guddina %519)** gaheera. 11. Zakaa fi Waqfi 🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺 Baankichi seenaa dhaabbata faayinaansii biyya keenyaa keessatti dura-bu'aa fi fageessee ilaalaa ta'uun, waggaa baajataa kanaan bu'aa waligalaa irraa Zakaa dhaabbataa Birrii miilioona 8 akkasumas Waqfiif Birrii miilioona 2 baasuun dirqama Shari'aa isaa bahachuu danda'eera. 12. Tajaajila Faayinaansii Bu'aa Malee Dhiyaate 🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 Baankiin keenya baankii sirna Shari'aa bu'uureffatee hojjetu akkuma ta'eetti, qajeelfama Maqaasid Al-Shari'aa qaama ergama daldala isaa gochuun, dhiyeessii pirojektoota waaraa fi itti-gaafatamummaa qaban irratti bu'aa tokko malee qard al-hasan (Benevolent Loan) kaffaltii faayinaansii isaa keessaa Birrii miilioona 341.72 (%2.03) tajaajila liqii kenneera. Tajaajila Haramayn: Baankiin Hijraa mu'uminitoota dandeettii maallaqaa dadhabanii hawwii guddaa hajjii gochuu qabaniif tajaajila addaa Haramayn qopheessuun, baasii deemsa kanaaf barbaachisu keessaa %50 tajaajila bu'aa malee (Qard al-Hasan) bifa liqiitiin dhiyeessee jira. Carraa addaa kanaan hanga xumura waggaa baajataa kanaatti mu'uminitoonni 35 abjuu jireenya isaanii mirkaneessuun sirna hajjii isaanii milkaa'inaan akka raawwatan taasisaniiru.
እንኳን ደስ አላችሁ! አልሀምዱሊላህ! Baga gammaddan! Alhamdulillaah! 🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 የሂጅራ ባንክ የዘንድሮ ዋና ዋና ስኬቶች Milkaa’ina Guddaa Baankii Hijraa Kan Bara Kanaa 💥💥💥💢💢💢🔥🔥🔥💢💢💢💢💢💢 1. አጠቃላይ ገቢ ✅✅✅✅✅✅ ባንኩ ከተመሠረተ ጀምሮ ባለፉት አራት ዓመታት ካስመዘገበው አጠቃላይ ድምር ገቢ (2.965 ቢሊዮን ብር) በመብለጥ የዘንድሮው ዓመታዊ ገቢው ብር 3.55 ቢሊዮን የደረሰ ሲሆን ይህም ቀደም ሲል ከነበረው በጀት ዓመት አንፃር የ97% ዕድገት አሳይቷል፡፡ 2. ጠቅላላ ትርፍ 🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹 ካለፉት አራት ዓመታት አጠቃላይ የትርፍ ድምር (820.7 ሚሊዮን ብር) ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ብልጫ በማሳየት 1.9 ቢሊዮን በማድረስ ባንኩ ካገኘው ትርፍ አንጻር በ132% የላቀ እድገት አስመዝግቧል፡፡ 3. የባንኩ አጠቃላይ የሀብት መጠን 🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 ባለፈው በጀት ዓመት ከነበረው 14.61 ቢሊዮን ብር በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ በ115% በማሳደግ ብር 31.45 ቢሊዮን ደርሷል። 4. ተቀማጭ ገንዘብ 💥💥💥💥💥💥💥 ባለፈው በጀት ዓመት በተመሳሳይ ወቅት ከነበረበት 11.94 ቢሊዮን ብር በመነሳት በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ በ101% በማሳደግ ብር 24 ቢሊዮን ማድረስ ተችሏል። 5. ጠቅላላ ካፒታል 🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺 ባለፈው በጀት ዓመት ከነበረበት ብር 2.42 ቢሊዮን በ 202% (ከ2 እጥፍ በላይ) በማሳደግ ብር 7.45 ቢሊዮን አድርሷል። 6. የውጭ ምንዛሬ ግኝት 🌰🌰🌰🌰🌰🌰🌰🌰 ባንኩ ባለፉት አራት ዓመታት በድምሩ ካንቀሳቀሰው የውጭ ምንዛሬ መጠን የ187.6% ዕድገት በማሳየት በበጀት ዓመቱ 158 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ማግኘት ችሏል፡፡ 7. ለደንበኞች የቀረበ ጠቅላላ የፋይናንስ መጠን 🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 ባለፈው በጀት ዓመት ከነበረው የብር 7.2 ቢሊዮን የፋይናንስ አቅርቦት በ133% በማሳደግ በበጀት ዓመቱ ብር 16.78 ቢሊዮን በላይ ፋይናንስ ያደረገ ሲሆን ይህም በሙሻረካ ብር 1.6 ቢሊዮን (9.54%)፣ በሙዳረባህ ብር 1.33 ቢሊየን (7.93%) እንዲሁም በቀርደል ሐሰን (ነፃ ብድር) ብር 341.72 ሚሊየን (2.03%) ፋይናንስ አገልግሎት አቅርቧል፡ 8. የቅርንጫፍ ብዛት 🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈 ባንኩ በበጀት ዓመቱ ውስጥ 41 አዳዲስ ቅርንጫፎችን በመክፈት አጠቃላይ የቅርንጫፎቹን ብዛት 170 አድርሷል። 9. ዲጂታል ፋይናንሲንግ 🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵 3,871 ለሚደርሱ በአነስተኛና መካከለኛ ሥራ ላይ ለተሰማሩ እንዲሁም ሴቶችና ወጣቶች ያለ ማስያዣ ብር 1.5 ቢሊየን የኢሙራበሃ ፋይናንሲንግ ማቅረብ ችሏል፡፡ 10. ዲጂታል ባንኪንግ ❄❄❄❄❄❄❄ ባንኩ በበጀት ዓመቱ የዲጂታል ባንኪንግ አጠቃላይ ደንበኞች ቁጥር 2.24 ሚሊዮን ማድረስ የቻለ ሲሆን አጠቃላይ በዲጅታል ባንኪንግ የገንዘብ ዝውውር መጠኑ ብር 41.72 ቢሊየን (የ86% ዕድገት) እንዲሁም የግብይት መጠኑ 261,982 (የ519% ዕድገት) ማድረስ ችሏል፡ 11. ዘካና ወቅፍ 🌺🌺🌺🌺🌺 ባንኩ በሀገራችን የፋይናንስ ተቋማት ታሪክ ፈር ቀዳጅ በመሆን በበጀት ዓመቱ ከአጠቃላይ ትርፉ ላይ ተቋማዊ ዘካ ብር 8 ሚሊየን እንዲሁም ለወቅፍ ብር 2 ሚሊየን በማውጣት ሸሪዓዊ ግዴታውን መወጣት ችሏል፡፡ 12. ያለትርፍ የቀረበ የፋይናንስ አገልግሎት 🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 ባንካችን ሸሪዓን መሰረት በማደረግ የሚሰራ ባንክ እንደመሆኑ መጠን የመቃሲድ አል ሸሪዓ መርህን የቢዝነሱ ተልዕኮ አካል በማድረግ ዘላቂነትና ኃላፊነትን መሰረት ያደረገ ኢንቨስትመንት ላይ ያለ ምንም ትርፍ በቀርድ አል-ሐሰን (Benevolent Loan ) ከፋይናንሲንግ ፖርትፎሊዮው ብር 341.72 ሚሊየን (2.03%) የሚደርስ የፋይናንሲንግ አገልግሎት ሰጥቷል፡፡ ሐረመይን አገልግሎት ፡ ሂጅራ ባንክ ሐጅ የማድረግ ታላቅ ምኞት ኖሯቸው የገንዘብ እጥረት ለገጠማቸው ምዕመናን ልዩ የሐረመይን አገልግሎት በማዘጋጀት ፣ ለጉዞው የሚያስፈልገውን 50% ወጪ ያለ ምንም ትርፍ (በቀርድ አል-ሐሰን) በብድር መልክ ማቅረብ ችሏል። በዚህም ልዩ ዕድል እስከተጠናቀቀው በጀት ዓመት ድረስ 35 ምዕመናን የዕድሜ ዘመን ህልማቸውን እውን በማድረግ የሐጅ ሥነ-ሥርዓታቸውን በስኬት እንዲፈጽሙ አስችሏል። Baga gammaddan! Alhamdulillaah! 🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 Milkaa’ina Guddaa Baankii Hijraa Kan Bara Kanaa 💥💥💥💢💢💢🔥🔥🔥💢💢💢💢💢💢 1. Galii Waligalaa ✅✅✅✅✅✅ Galiin waggaa kan bara kanaa, galii waligalaa baankichi erga hundaa’ee as waggoottan afran darban keessatti kuufama galee ture (2.965\text{ bilioona} birrii) caaluun Birrii bilioona 3.55 gaheera. Kunis waggaa baajataa darbe keessaa yoo ilaalamu guddina %97 agarsiisa. 2. Bu’aa Jumlaa 🌹🌹🌹🌹🌹🌹 Kuufama bu'aa waggoottan afran darbanii (820.7\text{ miilioona} birrii) irra birrii bilioona tokkoo ol caaluun, bu'aa isaa bilioona 1.9 irraan gaheera. Kanaanis baankichi bu'aa argateen guddina ol'aanaa %132 galmeessee jira. 3. Qabeenya Waligalaa Baankichaa 🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 Qabeenya waggaa baajataa darbe birrii bilioona 14.61 ture irraa waggaa tokko keessatti %115 guddisuun Birrii bilioona 31.45 irraan gaheera. 4. Quusannoo (Qorqortii) Maamiltootaa 💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥 Yeroo walfakkaataa waggaa baajataa darbe birrii bilioona 11.94 irra ture irraa ka'uun, waggaa tokko keessatti %101 guddisuun Birrii bilioona 24 irraan gahuun danda'ameera. 5. Kaapitaala Waligalaa 🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺 Kaapitaala waggaa baajataa darbe birrii bilioona 2.42 ture irraa %202 (dachaa lamaa ol) guddisuun Birr bilioona 7.45 irraan gaheera. 6. Argannoo Maallaqa Alaa (Forex) 🌰🌰🌰🌰🌰🌰🌰🌰🌰🌰🌰🌰🌰 Baankichi daldala maallaqa alaa waggoottan afran darban sochoosaa ture irra guddina %187.6 agarsiisuun, waggaa baajataa kanaan Doolara Ameerikaa miilioona 158 argachuu danda'eera.
без подписи
без подписи
የዓሹራእ ጾም ትሩፋት (ፈድል) ✅✅✅✅✅✅✅✅ የአቡ ቀታዳህ አል-አንሷሪ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ሐዲስ: حديث أبي قتادة الأنصاري رضي الله عنه: أن النبي صلى الله عليه وسلم سُئل عن صيام يوم عاشوراء، فقال: "يُكَفِّرُ السَّنَةَ المَاضِيَةَ" (رواه مسلم). ከአቢቀታዳ አል-አንሷሪ (ረ.ዐ) እንደተላለፈው የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ስለ አሹራ (የሙሐረም ወር 10ኛ ቀን) ጾም ተጠየቁ፡፡ “የአሹራ ቀን ጾም ያለፈውን ዓመት ወንጀል ያስምራል፡፡” ሲሉ መለሱ፡፡ (ሶሒሕ አል-ሙስሊም)፡፡ ሙስሊሞችም ሙሳና ተከታዮቹ በፊርዐውን ላይ ድል የተቀዳጁበትንና ነጻነታቸውን ያወጁበትን ቀን በጾም ያስታውሱታል፡፡ ታሪኩንም በማውሳት ይማማሩታል፡፡ የሙሳና ተከታዮቹ ድል የነርሱም ድል በመሆኑ፡፡ በአምባገነኑ ፊርዐውን ውድቀትም ይደሰታሉ፡፡ ምክንያቱም ፊርዐውን የአምባገነኖች ሁሉ ተምሳሌት ነውና፡፡
የድሉ ቀን ሲታወስ 🌰🌰🌰🌰🌰 የአሹራ ፆም የሚውለው በነገ ሀሙስ ነው። 🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮 ፈርዖን የአምባገነኖች ተምሳሌት ከተሰኘው የአሕመዲን ጀበል መጽሐፍ የተወሰደ) 🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆 ሙሴና ተከታዮቹ በፈርዖንና ወገኖቹ ላይ ድል የተቀዳጁበት ቀን ታላቅና ታሪካዊ ቀን ነው፡፡ ምክንያቱም የዘመናት ባርነት በነጻነት የተቀየረበት፤ በዳያቸውን ድል የነሱበትና ፈርዖን ከነአጋሮቹ የተንኮታኮተበት ዕለት ነው፡፡ በመሆኑም የድሉ ቀንና ታሪክ ሁሌም ሊታወስ ይገባዋል፡፡ ቀጣዩ ትውልድም ታሪኩን በጥሞና እንዲያውቅና እንዲማርበት ማስታወስ ግድ ይላል፡፡ በመሆኑም እንደ መጽሐፍ ቅዱስ ገለጻ አምላክ ሙሴን እንዲህ ብሎታል፦ “ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር ሙሴን ‘ዘወትር ሲታወስ እንዲኖር የዚህን ድል ታሪክ ጻፈው፤’ አለው፡፡” (ዘጸአት 17÷ 14) በፈርዖን ላይ የተቀዳጁትን ድል ለማስታወስ አምላክ ሁለት የበዓል ሥነ-ሥርዓቶችን እንደደነገገ መጽሐፍ ቅዱስ ይጠቅሳል፡፡ አንደኛው የፋሲካ መስዋዕት የሚደረግበት በዓል ሲሆን ይህም ቀን ፈርዖንን ለማንበርከክ የግብጻውያን የበኩር ልጆች የተገደሉበት (በዚያ) ሌሊት ነበር፡፡ ይህንኑ ሥርዓት ለእስራኤላውያን ቀጣይ ትውልድ ጭምር በቋሚነት እንዲቀጥል አምላክ ማዘዙን መጽሐፍ ቅዱስ ይጠቅሳል፡፡ እንዲህም ይላል፦ “ልጆቻችሁ ‘ይህ ሥርዓት ምንድን ነው’? ብለው በሚጠይቁአችሁ ጊዜ÷ እናንተም እንዲህ ብላችሁ ትመልሱላቸዋላችሁ፤ ‘ይህ እግዚአብሔርን ለማክበር የሚደረግ የፋሲካ መሥዋዕት ነው፤ እግዚአብሔር በግብጽ ምድር የእስራኤላውያን መኖሪያ ቤቶች አልፎ በመሄድ ግብጻውያንን ሲገድል እኛን አድኖናል፡፡’” (ዘጸአት 12÷26-27) እንደ መጽሐፍ ቅዱስ ገለጻ ይህ የድል ታሪክ በቀጣይ ትውልዶች ጭምር የተቀደሰ ተደርጐ ይታወሳል፡፡ ይህንኑ መጽሐፉ እንዲህ በማለት ይገልጻል፦ “እግዚአብሔር ሕዝቡን እየጠበቀ ከግብጽ ምድር ባወጣቸው ዕለት ጊዜው ሌሊት ነበር፤ ያም ሌሊት እስራኤላውያን በመጠባበቅ ተግተው የሚያድሩበት ለሚመጣው ትውልድ ሁሉ ለእግዚአብሔር የተቀደሰ ሌሊት ነው፡፡” (ዘጸአት 12÷ 42) ሌላኛው ከነጻነቱ ድል ጋር ተያይዞ በመጽሐፍ ቅዱስ የተጠቀሰው “የቂጣ በዓል” ነው፡፡ ይህ በዓል በዓመቱ የመጀመሪያ ወር ላይ የሚከበር ሲሆን ሰባት ቀናት ያክል እርሾ የሌለው ቂጣ የሚበላበት ነው፡፡ በሰባተኛው ቀንም የቂጣ በዓል ይደረጋል፡፡ ይህ የሚደረገው ከግብጽ የባርነት ሕይወት ነጻነት እንዲቀዳጁ አምላክ ያደረገላቸውን እገዛ ለማስታወስ ነው፡፡ ይህንኑ መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይገልጸዋል፦ “ሙሴም ለሕዝቡ እንዲህ አለ፦ ‘ይህ ቀን በባርነት ስትገዙ የኖራችሁበትን የግብጽን ምድር ለቃችሁ የወጣችሁበት ስለሆነ ይህን ቀን አስታወሱ፤ እግዚአብሔር በታላቅ ኃይሉ በመታደግ ያወጣችሁ በዚህ ቀን ነው፤’” (ዘጸአት 13÷3) ስለቂጣ በዓል አከባበርም መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይገልጻል፦ “በማርና በወተት ወደበለፀገችው ወደዚያች ለም ምድር በሚያገባችሁ ጊዜ በዓመቱ መጀመሪያ ወር ላይ ይህን በዓል ታከብሩታላችሁ፡፡ ሰባት ቀን ሙሉ እርሾ የሌለበት ቂጣ ትበላላችሁ፤ በሰባተኛውም ቀን ለእግዚአብሔር ክብር በዓል ታደርጋላችሁ፡፡ እስከ ሰባት ቀን ድረስ ያልቦካ እንጀራ ትበላላችሁ፤ እርሾም ሆነ የቦካ እንጀራ ከቶ በምድራችሁ አይገኝ፡፡ በዓሉም በሚከበርበት ጊዜ ይህን ሁሉ የምታደርጉት ከግብጽ በወጣችሁበት ጊዜ እግዚአብሔር ያደረገላችሁን መልካም ነገር ሁሉ ለማስታወስ መሆኑን ለልጆቻችሁ ተርኩላቸው፡፡ ይህም በዓል በእጃችሁ እንደታሰረ ምልክትና በግንባራችሁ እንዳለ ማስታወሻ ይሆንላችኋል፤ እግዚአብሔር በታላቅ ኃይሉ ከግብጽ ስላወጣችሁም የእግዚአብሔር ሕግ ዘወትር ከአንደበታችሁ ሳይለይ በቃላችሁ እንድትደግሙትና እንድታጠኑት ያስታውሳችኋል፡፡ ስለዚህ ይህን በዓል በየዓመቱ በተመደበለት ጊዜ የማክበር ሥርዓት ይሁንላችሁ፡፡” (ዘጸአት 13÷5-10) በዚህ መልኩ የድሉ ቀን እየታወሰ እንዲቀጥል መጽሐፉ ደንግጓል፡፡ ሙሳ (ዐ.ሰ) እና ተከታዮቹ ከፊርዐውን ጭቆናና ግፍ ነጻ የወጡበት ዕለት በኢስላምም ዘወትር ይታወሳል፡፡ ይህች ቀን ፊርዐውንና አጋሮቹ በባሕር የሰጠሙባት ዕለት ናት፡፡ በመሆኑም ይህች ታሪካዊ ዕለት በመሆኗም ሁሌም ልትታወስ ይገባታል፡፡ ይህችው ቀን በዚያው ዕለት አላህ በቁርኣን “ዛሬ” ብሎ የጠቀሳት ቀን ነች፡፡ በዚህችው ቀን ሙሳና ተከታዮቹ ለአምላካቸው የምስጋና ጾም እየጾሙ ዕለቷን ያስታውሱ ነበር፡፡ አምባገነኑን ፊርዐውንን አላህ በባሕር ሲያሰጥመው እንዲህ ነበር ያለው፦ فَٱلۡيَوۡمَ نُنَجِّيكَ بِبَدَنِكَ لِتَكُونَ لِمَنۡ خَلۡفَكَ ءَايَةٗۚ وَإِنَّ كَثِيرٗا مِّنَ ٱلنَّاسِ عَنۡ ءَايَٰتِنَا لَغَٰفِلُونَ — سورة يونس (10:92) “ዛሬ÷ ከአንተ በኋላ ለሚመጡ (ትውልዶች) ተአምር ትሆን ዘንድ አካልህን እናድናለን፡፡ ግና ብዙዎች ሰዎች ተአምራቶቻችንን ይዘነጋሉ፡፡” (ዩኑስ÷ 92) እንደ ኢስላማዊ መዛግብት ገለጻ ሙሳንና ተከታዮቹን አላህ ነጻ ያወጣበትና እንዲሁም “ዛሬ” ሲል አላህ የጠቀሳት ዕለት በኢስላማዊ አቆጣጠር በመጀመሪያ ወር (ሙሐረም) 10ኛ ቀን ነች፡፡ ከኢብኑ ዐብ-ባስ (ረ.ዐ) እንደተላለፈው ነቢዩ ሙሳና ተከታዮቹ ዕለቷን በጾም ያሳልፉ ነበር፡፡ የአላህ መልዕክተኛ ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ወደ መዲና ከተማ ባቀኑበት ጊዜ ዕለቷን አይሁዶች ሲጾሙ አገኙ፡፡ የሚጾሙበትንም ምክንያት ጠየቋቸው፡፡ እንዲህ በማለትም መለሱላቸው፦ “ይህ ታላቅ ቀን ነው፡፡ አላህ ሙሳንና ተከታዮቹን ያዳነው በዚህ ቀን ነው፡፡ የፊርዖንንም ቤተሰቦች ያሰመጠበት ዕለት ነው፡፡ ሙሳም አላህን ለማመስገን ዕለቱን ይጾም ነበር”፡፡ መልዕክተኛውም (ሰ.ዐ.ወ) “እኔ ከአይሁዶች ይበልጥ ለሙሳ የቀረብኩ ነኝ፡፡” በማለት ዕለቱን ይጾሙ ጀመር፡፡ ተከታዮቻቸውንም እለቱን እንዲጾሙ አዘዙ፡፡(ሶሒሕ አል-ቡኻሪ፣ጥሪዝ 4፣ ሐዲሥ ቁጥር 1130፣ ገጽ 795) ሙስሊሞችም ሁለቱ የአላህ መልዕክተኞች (ሙሳና ሙሐመድ) ሁለት ሺህ ዓመታት ገደማ ቢራራቁም የሙሳ ድል የነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ድል ነውና ዕለቱን በጾም አሳለፉ፡፡ ተከታዮቻቸውንም የድሉን ቀን በጾም እንዲያስታውሱ አዘዙ፡፡ ተከታዮቻቸው ዕለቱን (ሙሐረም 10ኛ ቀንን) እንዲጾሙ ያዘዙት እንዲህ በማለት ነበር፦ “ከነርሱ (ከአይሁዶቹ) ይልቅ ለሙሳ የምትቀርቡ እናንተ ናችሁ፡፡ እናም ዕለቱን ጹሙ፡፡”(ኢብኑ ከሢር፣ ተፍሲር አል-ቁርኣኑል ዐዚም፣ ጥራዝ 2፣ ገጽ 915) ይህ ሙስሊሞች የሚጾሙት ፆምም “የአሹራ ቀን ጾም” ተብሎ ይታወቃል፡፡ ዕለቱንም የሙሳንና የፊርዐውንን የትግል ታሪክ እያስታወሱ÷ ከታሪኩ በመማር የሙሳ ድል የነርሱም ድል እንደሆነ እያሰቡ ይጾማሉ፡፡ የፊርዐውን ውድቀትም የሁሉም እኩያንና መሰል አምባገነኖች ውድቅት እንዲሆን እየተመኙ፤ አላህ ሙሳንም እንደረዳ ሁሉ እነርሱንም እንዲረዳ ይማጸናሉ፡፡ ኢስላም እንደሚያስተምረው ዕለቱንም በጾም ማሳለፉ እጅግ ተወዳጅና ከፍተኛ ምንዳ የሚያስገኝ የአምልኮ ተግባር ነው፡፡
የዘንድሮ ዓሹራ ጾም የፊታችን ሀሙስ ሰኔ18 ነው የሚውለው። ቀኑን መፆሙ የ አንድ ዓመት ያለፈ ወንጀልን ያስምራል። ከፊት 9ነኛውን ቀንም መጾም ተወዳጅ ነው፤ ይህ ደግሞ ነገ ረቡዕ ሰኔ 17 ነው። አላህ ያግራልን።
9ኛ) ሼህ አሊዩ መሀመድ አህመድ ፦ አጣዬ ከተማ- መጋቢት 10 ቀን 2013 💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥 በአጣዬ ከተማ የአንሷር መስጂድ ኢማም የነበሩት ሼህ አሊዩ መሀመድ አህመድ (ሌሎች ሃፊዝ ሼህ ዘይኑ በማለጥ የጠቀሱም አሉ) እለተ አርብ መጋቢት 10 ቀን 2013 ከምሽቱ በ2፡00 ላይ የኢሻ ሰላትን አሰግደው ከአራት ደረሶቻቸው ጋር ወደ ቤት በመመለስ ላይ ሳሉ በአማራ ክልል ልዩ ኃይል ተገደሉ። ይህ ግድያ አሰቃቂ ድርጊት በአካባቢው ለተቀሰቀሰው መጠነ-ሰፊ ቀውስ ዋነኛ መነሻ ሆኗል። የግድያውን ዜና ተከትሎ የኢማሙን አስክሬን ለማንሳት የሞከሩ የከተማው ነዋሪዎች እና ወደ ስፍራው የተሰባሰቡ የገጠር የኦሮሞ ተወላጆች ላይ የክልሉ ልዩ ኃይልና ሚሊሻ ተኩስ መክፈታቸው ግጭቱን ይበልጥ አባባሰው። ሂዩማን ራይትስ ዎች (Human Rights Watch) በ2022 ዓለም አቀፍ ሪፖርቱ ላይ እንዳረጋገጠው፣ የጸጥታ አካላቱ በህዝቡ ላይ የወሰዱት የኃይል እርምጃ ውጥረቱን ወደ ታጠቀ የእርስ በርስ ጥቃት የለወጠው ሲሆን፣ ለቀናት በቀጠለው በዚህ አውዳሚ ግጭት ከተሞችና መንደሮች ወድመዋል፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ ንጹሃን ተገድለዋል፣ እንዲሁም ከ200,000 በላይ ዜጎች ተፈናቅለዋል። ሆኖም ይህ ሁሉ ጥፋት የደረሰ ቢሆንም፣ በወቅቱ በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨው የተዛባ ትርክት እውነተኛውን የግጭት መነሻ በመደብቅ፣ የሟቹን ኢማም ማንነት «አንድ ግለሰብ» በሚል በመደበቅ ጥቃቱ ሙሉ በሙሉ በ"ኦነግ ሸኔ" እንደተፈጸመ አስመስሎ በማቅረብ ሀቁን ለማድበስበስ የሞከረ ነበር። ሆኖም ግጭቱን ለማረጋጋት መከላከያ ከገባ በኋላ ጄነራል ባጫ ደበሌ በሰጡት መግለጫ መነሻው የኢማም መገደል መሆኑን በመግለጫቸው ላይ አንስተዋል። 10ኛ) ሼህ ኡመር ሀጂ ሀሰን፦ ሸዋ ሮቢት- መጋቢት 12 ቀን 2013 📕📕📕📕📕📕📕📕📕📕📕📕📕 ሼህ ኡመር ሀጂ ሀሰን በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ጋንጋሃ ቀበሌ በተባለ ስፍራ ይኖሩ የነበሩ የ40 ዓመት እድሜ ላይ ይገኙ የነበሩ ዓሊም ሲሆኑ በመጋቢት 12 ቀን 2013 በቀይ መስቀል አምቡላንስ በመጓዝ ላይ እያሉ በሸዋ ሮቢት ከተማ ውስጥ በአማራ ልዩ ሃይል አባላት እና የፋኖ ታጣቂዎች በከፈቱት ጥቃት ከሌሎች ታካሚዎች ጋር በጥይትና በስለት ተደብድበው ተገድለዋል። ስለጉዳዩ «ዘ ሂዩማን ራይትስ ሊግ ኦፍ ሆርን ኦፍ አፍሪካ» በአፕሪል 6 ቀን 2021 «Ethiopia: Appeal for Urgent Independent Investigation into Shewa Robit Massacre of March 21, 2021!» በሚል ባወጣው መግለጫ ላይ የሼህ ኡመርን ሞት ጠቅሷል። 11ኛ) ሼይኽ አሊይ ሀሰን፦በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን ሰንበቴ ከተማ-ሚያዚያ 9 ቀን 2013 🔵🔵🔵🔵🔵🔵🔵🔵🔵🔵🔵🔵🔵 በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን ሰንበቴ ከተማ አስተዳደር የቢላል መስጂድ ኢማም የሆኑት ሼይኽ አሊይ ሀሰን ሚያዚያ 9 ቀን 2013 መገደላቸውን የሃሩን ሚዲያ በአፕሪል 18 ቀን 2021 እንዲህ በማለት ዘግቦ ነበር፦ «በሰንበቴ ከተማ የቢላል መስጂድ ኢማም የሆኑት ሼይኽ አሊይ ሀሰን በትላንትናው ዕለት መገደላቸውን የሀሩን ምንጮች አሳውቀውናል። ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን»። የሃሩን ሚዲያ የፌስቡክ ዘገባ በማንና እንዴት እንደተገደሉ የማያብራራ ሲሆን በኦሮምኛ ስለጉዳዩ የጻፉ ጥቂቶች ግን በመከላከያ ሠራዊት መገደላቸው ጠቅሰው ነበር። ሌሎች የአይን እማኞች ደግሞ ገዳዮቹ የፌደራል ፖሊስ ልብስ የለበሱ የልዩ ሃይል አባላት እንደሆኑ ገልጸው ኢማሙ በረመዳን ወር የመግሪብ ሶላትን አሰግደው ወደ ቤታቸው በመመለስ ላይ ሳሉ፣ በመስጂዱ በር ላይ ህይወታቸው መቀጠፊን ጽፈዋል። ሃሩን ሚዲያም ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ በለጠፈው ተጨማሪ ጽሑፍ «ኢፌድሪ መከላከያ ሚኒስትር ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ቤተ-ክርስቲያናት ፣የግለሰቦች ቤቶች ፣የመንግስት መስሪያ ቤቶች ጥቃት እንዳይደርስባቸው በሚል ማስጠንቀቂያ ሲሰጥ ስለመስጅድ ግን ምንም ያለው ነገር የለም። በነበረው ግጭት መስጅድ እንደተቃጠለ ኢማም እንደተገደለ እንኳን እየታወቀ ሙስሊሙ ላይ የሚደርስ በደል ግን እምብዛም ትኩረት ተሰጥቶት በመንግስት ደረጃ አልተገለፀም። የመስጅድ ኢማምን መገደል ስንዘግብ የተቃወማችሁ ሙስሊሞች መልዕክቱ ከማንም በላይ ለናንተ ነው። ቢያንስ ግራ በሚያጋባው የሀገራችን ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ምንም ማለት ባንችል ከበደሎች መሀል የማናቸውም የሙስሊሞች በደል ተሸሽጎ እንዳይቀር በማሰብ ነው የደረሰንን የተጣራ መረጃ መሠረት አድርገን ዘገባውን የሰራነው። በየትኛውም አካባቢ የሚደርሱ የሙስሊሙ በደሎች አሁንም ወደፊትም ያሳስቡናል፤ እንደ ሚዲያ ዋነኛ የትኩረት አጀንዳዎቻችንም ናቸው። በዚህ ስራ ላይ ሁሉንም አካል ማስደሰት አይቻልም። የደረሰንን ከዚያም ያረጋገጥነውን መረጃ ግን ወደናንተው እናደርሳለን።» 12ኛ) ሼህ አዱላይ፦አፋር ክልል ፈንቲ ረሱ ዞን ያሎ ወረዳ- 2013 መጨረሻ 💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥 የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን(ኢሰመኮ) ባወጣው ሪፖርት እንደገለጸው የ80 ዓመት አዛውንት የነበሩት ሼህ አዱላይ የተገደሉት በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ወቅት በ2013 መጨረሻ ወይም 2014 መግቢያ ላይ በአፋር ክልል ፈንቲ ረሱ ዞን ያሎ ወረዳ ጎቢዶራ ከተማ ውስጥ በነበሩ የትግራይ ኃይሎች(ሕወሃት) ታጣቂዎች መስጂድ ውስጥ እንዳሉ ነበር በጥይት የተገደሉት። (Report on Violations of Human Rights and International Humanitarian Law in Afar and Amhara Regions of Ethiopia) 13ኛ) ሼህ ሰማን አደም፦ ሰሜን ጎንደር ዞን አድርቃይ-ከሐምሌ 17 ቀን 2013 በኋላ ❗❗❗❗❗❗❗❗❗❗❗❗ ከሐምሌ 17 ቀን 2013 ዓ.ል. ጀምሮ የሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ወራሪ ኃይል በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን የምትገኘውን የአደርቃይ ወረዳን በኃይል ተቆጣጥሮ ነበር። ሕወሓት በአካባቢው ላይ በቆዩባቸው ወራት ውስጥ በንጹሃን ዜጎች ላይ እጅግ አሰቃቂ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን እና የታገቱ ግድያዎችን ፈጽመዋል። በዚህ የጥፋት ዘመቻ ከተገደሉ በርካታ ንጹሃን መካከል ዕድሜያቸው 54 ዓመት የነበሩት ታዋቂው የሃይማኖት አባት ሼህ ሰማን አደም አንዱ ነበሩ። የአማራ ማኅበር በአሜሪካ (AAA) ባጠናቀረው ሪፖርት መሠረት፥ ሼህ ሰማን አደም በሕወሓት ታጣቂዎች አማካኝነት በግፍ እንዲገደሉ የተደረገው በሃውዛ ቀበሌ ውስጥ ነበር። ይቀጥላል...
በበጎ ተግባራቸው ትልቅ ዕውቅናና ተሰሚነት የነበራቸው የእኝህ ታላቅ ሼኽ በሁከት ውስጥ መገደል በማህበረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ሐዘን የፈጠረ ሲሆን፤ ግድያውን በተመለከተም የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ እና የተለያዩ የሀገር ውስጥ የዜና አውታሮች ይፋዊ ማረጋገጫ ሰጥተውበታል። 2012 ዓመተ ልደት ⭕⭕⭕⭕⭕⭕ 3ኛ) ኡስታዝ ሐምዛ፦ አዲስ አበባ -ጥቅምት 14 ቀን 2012 ዓ.ል. 💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢 በወቅቱ በጥቅምት 14 ቀን 2012 ዓ.ል. አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኘው የሸይኽ ሙሐመድ ሓሚዲን መርከዝ የዲን ተማሪ የሆኑ አምስት ደረሶች፤ የዶክተር ጄይላንን ደርስ (ሃይማኖታዊ ትምህርት) ለመካፈል ወደ አየር ጤና አቅንተው ነበር። ትምህርታቸውን አጠናቀው በእግር ሲመለሱም፣ በጀሞ መስታወት ፋብሪካ ‘ቻይና ካምፕ ማርያም ቤተክርስቲያን’ አካባቢ ዘግናኝ ጥቃት ተፈጽሞባቸዋል። ወጣቶቹ በመንገድ ላይ እያለፉ በኦሮምኛ ቋንቋ በመነጋገራቸው ብቻ፣ በዚያ አካባቢ የነበሩ ከ50 በላይ የሚሆኑ የጋሞ እንደሆኑ በንግግራቸው የተገመቱ ወጣቶች በጋራ ከበው በዱላና በተለያዩ መሣሪያዎች በጭካኔ ደብድበዋቸዋል። በዚህ የጅምላ ድብደባ ምክንያት ከተማሪዎቹ መካከል ኡስታዝ ሐምዛ ወዲያውኑ ሕይወቱ ያለፈ ሲሆን፤ አስክሬኑም በክብር ተሸኝቶ ወደ ትውልድ ስፍራው ወደ ጅማ ተልኳል። በወቅቱ ከሰማዕቱ ኡስታዝ ሐምዛ ጋር የነበሩት አራት ወንድሞች ማለትም፦ አብዱልከሪም፣ አሚን ሷፊይ፣ ኢብራሂም ሲራጅ እና ኡስታዝ ሁሴን ክፉኛ ቆስለው በሕክምና ላይ ቆይተዋል። በወቅቱ በጉዳዩ ላይ ሃሩን ሚዱያና ራዲዪ ነጋሺን ጨምሮ ሙስሊም አክቲቪስቶች ዘገባ ሰርተው ነበር። 4ኛ) ሼኽ ኡመር ሱለይማን፦ አሳሳ ከተማ -ነሐሴ 12 ቀን 2012 ዓ.ል. 🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን አሳሳ ከተማ፣ ሼኽ ኡመር ሱለይማን የተባሉ ኢማም በነሐሴ 12 ቀን 2012 ዓ.ል. የአስር ሰላት አሰግደው ወደ ቤታቸው እንዳቀኑ፤ በኦሮሚያ ክልል ፖሊስ አካላት በመኖሪያ ቤታቸው ላይ በተከፈተ የጥይት እሩምታ ከነአራስ ባለቤታቸውና ከሦስት ወር ሕጻን ልጃቸው ጋር በግፍ ተገደሉ። በወቅቱ የኢማሙ መኖሪያ ቤት ቆርቆሮ በ28 ጥይቶች ተበሳስቶ ተገኝቷል። በስፍራው የነበሩት ሼኽ ቃሲም አብዱረሺድ የተባሉት ዓሊም ደግሞ እግራቸውን ተመተው ቆስለዋል። በያኔው የኦሮሚያ መጅሊስ ፕሬዝዳንትና በአሁኑ የፌዴራል መጅሊስ ፕሬዝዳንት ሼኽ ሐጂ ኢብራሂም የተመራና ዶ/ር ጄይላን ከድር፣ ሼኽ ሱልጣን ሐጂ አማን እንዲሁም የመጅሊስ የቦርድ አባላት የተካተቱበት ልዑክ በነሐሴ 15 ቀን 2012 ዓ.ል. ወደ ስፍራው አቅንቷል። ልዑኩ የኢማሙን ቤተሰቦች ድንገተኛ ለቅሶ ከደረሰ በኋላ፣ የአካባቢውን ማህበረሰብ በማናገር ጥቃቱን የፈጸሙት ስምንት የክልሉ ፖሊሶች መሆናቸውን በቦታው አረጋግጧል። የልዑካን ቡድኑ ከስፍራው ሲመለስም በጉዳዩ ላይ ከኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር አራርሳ መርዳሳ ጋር ውይይት ያደረገ ሲሆን፤ በወቅቱ ስለ ግድያው የሚያጣራ አካል ተቋቁሞ እንደሚመረመር ቢገለጽም፣ ጉዳዩ የውሃ ሽታ ሆኖ ቀርቷል። እኔም ይህንን ዘገንን ክስተት በወቅቱ በዚሁ የፌስቡክ ገጼ ላይ ለጥፌው ነበር። ስለ ጉዳዩ ‘ሃሩን ቲዩብ’ የልዑካኑን ቡድንና የሟች ቤተሰቦችን ጭምር ቃለ-መጠይቅ አድርጎ የሠራቸው እውነታውን የሚያጋልጡ ቪዲዮዎች ዛሬም ድረስ በዩቲዩብ (YouTube) ላይ ይገኛሉ። 5ኛ) ሸይኽ አብዱላሂ ከቢራ ፦ ሀረርጌ በዴሳ-ነሐሴ 16 ቀን 2012 💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢 በምዕራብ ሐረርጌ ዞን በደሳ ከተማ የተቅዋ መስጂድ ኢማም የነበሩት ሸይኽ አብዱላሂ ካቢራ ነሐሴ 16 ቀን 2012 ዓ.ል አብዱልሀሚድ በተባለ የ10 ዓመት ታዳጊ ቀብር ሲመለሱ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በጥይት ተመትተው ተገደለዋል። በወቅቱ አብሯቸው የነበረው ቱራ መሐመድ የተባለ ወጣትም ቆስሎ ነበር። በወቅቱ በነሐሴ 18 ቀን 2012 የኦሮሚያ መጅሊስ በሰጠው መግለጫ ግድያውን አውግዞ ጉዳዩ እንዲጣራና ገዳዮቹ ለፍርድ እንዲቀርቡ ጠይቆ እኔም በዚሁ የፌስቡክ ገጼ ላይ አጋርቼው ነበር።ዜናውን ሃሩን ቲዩብ ዘግቦት የነበር ሲሆን አሁንም ቪዲዮውም በዩቲዩብ ላይ ይገኛል።እኔም በጊዜው የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ለሆኑት ለአቶ ሽመልስ አብዲሳ በመደወል ስለጉዳዩ አናግሬያቸው ነበር።"ጉዳዩን አጣርተን እርምጃ እንወስዳለን" የሚል ምላሽ ሰጥተውኝ ነበር።ይህም የዉሃ ሽታ ሆኖ ቀረ። 6ኛ) ኡስታዝ አብዱልከሪም አሚን፦ አሳሳ ከተማ-12/12/2012 ⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕ ኡስታዝ አብዱልከሪም አሚን የተገደለው በአሳሳ ከተማ በነሐሴ 12 ቀን 2012 ነበር። በግድያው የተፈጸመው በቤታቸው ውስጥ ከነባለቤታቸውና አራስ ልጃቸው ከተገደሉት ኢማም ሼህ ዑመር ሱለይማን ጠዊል በተጨማሪ የአስር ሰላት አሰግደው ሲወጡ መስጅዳቸው በራፍ ላይ በወታደሮች በጥይት የተመቱት ሼህ ቃሲም ረሻድ የተሰኙት የጃሚዓልከቢር ምክትል ኢማም በኦሮሚያ ክልል ልዩ ኃይል በጥይት ሲመቱ እርሳቸውን ከወደቁበት ለማንሳት በሞከረበት ጊዜ በርሰ ላይ በተከፈተበት የተኩስ እሩምታ ነበር። በጊዜው የሃሩን ሚዲያ እንደዘገበውና የኦሮሚያ መጅሊስ እንዳረጋገጠው ኡስታዝ አብዱልከሪም ወዲያው ሕይወቱ ሲያልፍ ሼህ ቃሲም ረሻድ በሕክምና ሲረዱ ነበር።ይህን ጽሁፍ ለመጻፍ ስነሳ ወደ አሳሳ በመደወል እንዳረጋገጥኩት ሼህ ቃሲም ረሻድ ድነው በህይወት ይገኛሉ። 2013 ዓመተ ልደት 🔴🔴🔴🔴🔴🔴 7ኛ) ኢማም ሸህ ሰዒድ ፦ ቤንች ሸኮ ዞን ጉራፈርዳ ወረዳ ሹቢ ቀበሌ-ጥቅምት 14 ቀን 2013 💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢 በደቡብ ክልል ቤንች ሸኮ ዞን ጉራፈርዳ ወረዳ ሹቢ ቀበሌ ውስጥ ጥቅምት 14 ቀን 2013 ዓ.ል.ምሽት "ማንነታቸው ባልታወቀ" በተባሉ ታጣቂዎች በድንገት በተከፈተ የተኩስ እሩምታ የመስጂድ ኢማም የነበሩት ሸህ ሰዒድ በመኖሪያ ቤታቸው ኸልዋ ውስጥ ሳሉ በጥይት ተመተው ተገደሉ። ከርሳቸው ጋር ነፍሰጡር ባለቤታቸው ወ/ሮ ፉጡሬም በስለት አንገቷ ታርዶ በልቧ ተደፍታ ሞታ ተገኘች።ከነርሱ በተጨማሪም አንድ ህጻንን ጨምሮ 12 ንጹሃን አርሶ አደሮች በየቤታቸው ባሉበት በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል። 8ኛ) ደረሳ ሰዒድ ኢብራሂም ፦ ወረዳ ጃራገዶ ከተማ - ጥር 16 ቀን 2013 ⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕ በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን ምዕራብ እስቴ (አዳቤት) ወረዳ ጃራገዶ ከተማ አጠገብ፣ ከጦላይ ተነስቶ ከ1000 ኪሎ ሜትር በላይ በስደት የተጓዘውና ዕድሜው ከ15 ዓመት የማይበልጠው ታዳጊ ሙሳፊር ደረሳ ሰዒድ ኢብራሂም ጥር 16 ቀን 2013 ዓ.ልበደረሰበት አሰቃቂ የጅምላ ድብደባ ሕይወቱ አልፏል። ታዳጊውና ጓደኞቹ መንገድ ላይ በሰዎች ታፍነው ወደ አቅራቢያ ቤተ-ክርስቲያን እንዲገቡ ከተደረገ በኋላ በተፈጸመባቸው አረመኔያዊ ድብደባ ሰዒድ ወዲያውኑ ሕይወቱ ሲያልፍ፣ ሁለተኛው ደረሳ በከባድ ጉዳት ሆስፒታል ገብቷል፤ ሌሎቹ 15 ደረሳዎችም ከፍተኛ ድብደባ አስተናግደዋል። ሃሩን ሚዲያ በጊዜው እንደዘገበው ይህንን ግድያ ተከትሎ በጥሩንባ ጭምር ሰዎችን በመቀስቀስ በንጹሐን ሙስሊሞች መኖሪያ ቤቶች፣ መስጂዶችና የንግድ ሱቆች ላይ መጠነ-ሰፊ ቃጠሎና ዘረፋ ተፈጽሟል። የሟቹ ደረሳ አስክሬን ወደ ጅማ ዞን ጦላይ ወረዳ ወደ ቤተሰቡ ተወስዶ ተቀብሯል።ሃሩን ሚዲያ የቀብር ስነስርዓቱን ከመዘገብ በተጨማሪ፣ ቤተሰቦቹን ቃለመጠይቅ አድርጓል።ገንዘብ በማሰባሰብም እንዲረዱ አድርጓል።
ይህ ጽሑፍ ከጥቃቶቹ ዘርፎች አንዱ የሆነውን የኢማሞች ግድያ ለናሙናነት ብቻ በማንሳት፣ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን መከራና የትዕግስት ልክ በተግባር ለማሳየት ይሞክራል። በተመሳሳይ መልኩ፣ እኔ በየካቲት 7 ቀን 2010 ዓ.ል. ከእስር ቤት ከተፈታሁ ጀምሮ ባለፉት ስምንት ዓመታት ብቻ ያስተናገድናቸውን የመስጂዶች ቃጠሎና መፍረስ፣ የአማንያን ጥቃትና ግድያ፣ በየስድስት ወሩ የሚለኮሰውን የሙስሊም ተማሪዎች መከራ ወዘተ እያልን በየዘርፉ የሆነውንና እየሆነብን ያለውን ብናነሳ፤ ከዚህ ጽሑፍ በብዙ እጥፍ የሚበልጡ ዘለግ ያሉ በርካታ ጽሑፎች ወይም መጻሕፍት ይወጣቸዋል። በእርግጥ እንደ ማህበረሰብ የታገስነው ጨለምተኛ ስላልሆንንና ሀገሪቱ ያለችበትን ፈታኝ ሁኔታ ከመረዳት በመነጨ እንጂ፣ በማንኛውም አጀንዳ ዙሪያ ተደራጅተው ከሚታገሉት ሁሉ የላቁ በርካታ ማታገያ አጀንዳዎችም ሆነ የትግል ልምድ አጥተን አይደለም። ሆኖም ይህንን ሁኔታ በጥልቀት እያወቁና ራሳቸው የብዙዎቹ ጥቃቶች ጠንሳሾች ሆነው ሳለ፣ «ወሃቢያ» እና «ስልጤ» በሚሉ የፍረጃ ታፔላዎች «የኦርቶዶክስ ክርስቲያኑ ማህበረሰብ፣ የችግሮቹና የጥቃቶቹ ምንጭ ሁሉ ሙስሊሞች ናቸው» የሚል እምነትና ምስል ለመፍጠር እየሄዱበት ያለውን ርቀት ስናይ፤ የጸረ-ሙስሊም ዘመቻ አድራጊዎች እውነትን ከመቅበር ጀምሮ እስከ ተገላቢጦሽ ፍረጃ ድረስ ምን ያህል ርቀት እንደሚጓዙ ግልጽ ሆኖ ይታያል። ከ2010 ጀምሮ ለማሳየት የተሞከረው ጥቃቶቹ የግድ አሁን በስልጣን ላይ ካለው መንግስት ጋር ስለሚያያዝ ሳይሆን እኔ አሁን ባለኝ የፌስቡክ ገጼ መጻፍ ከጀመርኩበት ጊዜ ጀምሮ በቀጥታ ያወቅናቸውና በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ድምጽ ለመሆንም ሆነ ለማገዝ ጥረት ያደረግንባቸው ስለሆነና በቂ መረጃዎች ስላሉን ጭምር። በተጨማሪም ይህን ጽሑፍ ለመጻፍ ስነሳ ስህተት እንዳልሰራ የራሴን የቀድሞ የፌስቡክ ጽሁፎችን፥ የሃሩን ሚዲያ ዘገባዎችን፥ የመጅሊስ መግለጫዎችን ፥ የዩቲዩብ ቪዲዮዎችንና የሰብዓዊ መብት ሪፖርቶችን ዳግም ተመልክቻለሁ። እነዚህ ንጹሐን የሃይማኖት አባቶች ናሕይወታቸውን ያጡት በወቅቱ እንደተዘገበው በጽንፈኛ የፋኖ ታጣቂዎች፣ በትግራይ ኃይሎች (ሕወሓት)፥ በኦነግ ሸኔ፥ በኦሮሚያ ፖሊስ፥ በአማራ ክልል ልዩ ኃይል፥ ወዘተ በተፈጸሙ ዘግናኝ ጥቃቶች፣ የጅምላ ድብደባዎችና የአፈና ድርጊቶች ነው። ጥቃቶቹ የተፈጸሙት መስጂዶች ውስጥ፣ በመኖሪያ ቤቶቻቸው ኸልዋ፣ በአምቡላንስ ጉዞ ላይ ወይም ከሰላት መልስ ወደ ቤታቸው ሲያቀኑ ሲሆን፣ አብዛኛዎቹ ድርጊቶች ከታቀደ የጥላቻ ዘመቻ ዉጤት ናቸው። ይህ ጽሑፍ ከጥላቻው ዘመቻ መፋፋም በኋላ በዚህ ሳምንት የተገደሉትን ሁለት ደረሶችን ጨምሮ የ28 ኢማሞችን፥ ሼኮችን፥ኡስታዞችንና የዑለሞነን ግድያ የሚያትት ነው። ጽሑፉ አልበዛምን? 🔴🔴🔴🔴🔴🔴 ይህ ባለ 8 ገጽ ጽሑፍ በሁለት ክፍል ተቀረበ፤ ከ2010 ዓ.ል. ጀምሮ እያወቅናቸው፣ እዚሁ የፌስቡክ ገጻችን ላይ ስለ እነርሱ እየጻፍንና «ፍትህ!» እያልን የጮህንላቸውን፣ ነገር ግን ተራ በተራ ያጣናቸውንና እስካሁንም ፍትህ ያጡትን ኢማሞች፣ ዓሊሞች፣ ኡስታዞች፣ ዳኢዎችና ደረሶች በየዓመቱ የደረሰባቸውን ጥቃትና ግድያ ከነቀኑና ከነቦታው በዝርዝር የሚያብራራ ነው። እዚህ ላይ የተጠቀሱት በሙሉ እያንዳንዳችን በማህበራዊ ሚዲያችን የጮህንላቸው፣ እንደ ‘ሃሩን ሚዲያ’ ያሉ የሙስሊሙ ባለውለታ ሚዲያዎች ሳይሰለቹና ዋጋ ከፍለው የዘገቡልን፣ እንዲሁም የእያንዳንዳቸው ምስልና ቪዲዮ ዛሬም ድረስ በዩቲዩብ (YouTube) ላይ የሚገኝና ተመልሶ ማመሳከር የሚቻልባቸው እውነታዎች ናቸው። ከፊሎቹ ደግሞ የፌዴራልና የክልል መጅሊሶች በይፋ መግለጫ ያወጡባቸው ክስተቶች ናቸው። ይህንን ሁሉ ለመገንዘብና ለማንበብ ሞራሉ ከሌለህ፤ ስለ ዲኔ፣ ስለ ኢማሜ፣ ስለ ዓሊሜና ስለ ሙስሊሙ መብት የመቆርቆር መብት የለህም! ምክንያቱም አንተ በዚህ በተደራጀ መልኩ ቀስ በቀስ እየተገዘገዝክ ለመጠቃት ራስህን አመቻችተህ የተኛህ ነህና። ስለዚህ፦ አንብብ፤ ለሌሎች አጋራ፤ አስተያየትህንም ስጥበት! በአንተ አካባቢ ተገድለው በዚህ ጽሑፍ ውስጥ ያልተካተቱ ኢማሞችና ዓሊሞች ካሉ በአስተያየት መስጫው (Comment section) ላይ አካትታቸው። እንዲሁም በዚህ ጽሑፍ ውስጥ ስማቸው ተነስቶ ፎቶግራፋቸው ያልተካተተላቸው ሰማዕታት ካሉ ፎቶግራፋቸውን ከሥር ለጥፍ። ነቃ በል! መልካም ንባብ። በኢትዮጵያ አቆጣጠር 2010 ዓመተ ልደት 📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶 1ኛ) ኡስታዝ ጣሂር አወል፦ ሳጃ ከተማ - ሐምሌ 4 ቀን 2010 ዓ.ል. 💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥 በወቅቱ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል አካል በነበረው የየም ልዩ ወረዳ፣ ሳጃ ከተማ ውስጥ ለመስጂድና ለመድረሳ መገንቢያ የሚሆን ቦታ መጋቢት 16 ቀን 2009 ዓ.ል. በሺህ የሚቆጠር ሕዝብ በተገኘበት በይፋ ተሰጥቶ መሠረት ተጥሎበት ነበር። ሆኖም የነዋሪውን መብት የረገጡት የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ይሁን አሰፋ፣ በሐምሌ 4 ቀን 2010 ዓ.ል. «መድረሳው ሕገ-ወጥ ነው፤ መቼም ሊከፈት አይችልም» በማለት ለመድረሳውና ለመስጂዱ የተሰጠውን ይዞታ ቆርጠው ለግለሰቦች ለማከፋፈል ተነሱ፤ በሕዝቡ ላይም ዛቱ። ይህንን ተከትሎ ማህበረሰቡ መብቱን ለማስከበር ከፍተኛ ሕዝባዊ ተቃውሞ አደረገ። በዚህ ወቅት ፖሊስ በሰላማዊው ሕዝብ ላይ ድብደባና ተኩስ በመክፈቱ፣ ኡስታዝ ጣሂር አወልን ጨምሮ በርካታ አማኞች ተገድለዋል፤ ሌሎች በርካቶችም ቆስለዋል። ከግድያው በኋላ የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ይሁን አሰፋ ተጠያቂነትን ለማምለጥ፤ «ማንም ፖሊስ ሰውን አልገደለም፤ የሞተው ልጅ (ኡስታዝ ጣሂር) በድንጋይ ተደብድቦ ነው የሞተው» በማለት በሕዝብ ፊት የሐሰት ክህደት ሰነዘሩ። የወንጀል አሻራቸውን ለመቀየርና እውነታውን ለማስቀልበስም፣ የተፈጠረውን ግጭት በሙስሊሞችና በክርስቲያኖች መካከል እንደተደረገ አስመስለው ለክልሉ መንግሥት የሐሰት ሪፖርት አቀረቡ። የኡስታዝ ጣሂርን መገደል ተከትሎ የተነሳውን ሕዝባዊ ቁጣ ለመቆጣጠር ከወልቂጤ ከተማ የደረሰው ተጨማሪ የጸጥታ ኃይል ከተማዋን በቁጥጥር ሥር ያዋለ ሲሆን፤ በርካታ ንጹሐን ሙስሊሞችን በጅምላ እየለቀሙ ‘ፎፋ’ ወደተባለችው ከተማ በመውሰድ አሰቃቂ እስራት፣ እገታና እንግልት ፈጽመውባቸዋል። 2011 ዓመተ ልደት 💢💢💢💢💢💢 2ኛ) ሼኽ አህመድ አብዱል፦ ጅግጅጋ -ጥቅምት 21 ቀን 2011 ዓ.ል. 🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 በሶማሌ ክልል ዋና ከተማ ጅግጅጋ ውስጥ፣ ረቡዕ ጥቅምት 21 ቀን 2011 ዓ.ል. በድንገት ባገረሸው መጠነ-ሰፊ ሁከትና ብጥብጥ ሳቢያ፤ ታዋቂው የሃይማኖት አባት ሼኽ አህመድ አብዱል በጸጥታ ኃይሎች በተከፈተ አሰቃቂ የተኩስ እርምጃ ሕይወታቸውን በግፍ አጥተዋል። ግጭቱ ሊቀሰቀስ የቻለው በከተማዋ ቀበሌ 04 ፖሊስ ጣቢያ አካባቢ በቁጥጥር ሥር ውለው በታሰሩ ወጣቶች ምክንያት በተነሳ ሕዝባዊ ተቃውሞ ሲሆን፤ በዕለቱ የጸጥታ ኃይሎች ሁኔታውን ለመቆጣጠር በከፈቱት በራሪ ጥይት ሼኽ አህመድ አብዱል እና ሌላ ሰላማዊ ግለሰቦች ተመተው ወዲያውኑ ሕይወታቸው አልፏል። ይህ አሳዛኝ ክስተት የተፈጸመው፣ የቀድሞው የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አብዲ መሐመድ ዑመር (አብዲ ኢሌ) ከሥልጣን መነሳት ማግስት በክልሉ ተከስቶ በነበረው ከፍተኛ የፖለቲካ ሽግግር፣ የኃይል ክፍተትና አጠቃላይ የጸጥታ መቃወስ ወቅት ነበር።
የ28ቱ ኢማሞች ግድያ እና የተገላቢጦሽ ፍረጃ 🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 በአሕመዲን ጀበል፣ክፍል አንድ ✅✅✅✅✅✅✅✅✅ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ላለፉት በርካታ ዓመታት በአካላቸው፣ በእምነት ተቋማቶቻቸውና በማንነታቸው ላይ የሚፈጸሙትን ሁሉን አቀፍ ጥቃቶች፣ ግድያዎችና መዋቅራዊ በደሎች በሆደ-ሰፊነትና ለሀገር ሰላም ቅድሚያ በመስጠት በትዕግስት ሲያሳልፉ ቆይተዋል። በደል አድራሾቹን በጅምላ ከመክሰስና ወንጀሉን ማህበረሰባዊ መልክ ከመስጠት ይልቅ፣ ድምፃቸውን ለፍትህ ብቻ በማሰማት የበኩላቸውን ሀገራዊ ኃላፊነት ተወጥተዋል። ሆኖም ግን፣ ከእነዚህ አሰቃቂ ጥቃቶች ጀርባ ያሉና ለሙስሊሙ መከራ ዋና ተጠያቂ የሆኑ የጥላቻ ልሳናት፤ በተደራጀ የሚዲያ ዘመቻ እውነተኛውን ተበዳይ መልሰው አጥቂና ወንጀለኛ አድርገው የሚፈርጁበትን የተገላቢጦሽ የፕሮፓጋንዳ ስልት በስፋት እየተገበሩ ይገኛሉ። በተለይ በቅርቡ በአርሲ ከተፈጸመው ጥቃት ማግስት የታየው ጸረ-ሙስሊም የሚዲያ ትንኮሳና የሀሰት መቀናበር፤ እነዚህ ፅንፈኛ አካላት በሀገሪቱ ውስጥ መጠነ-ሰፊ የሃይማኖት ግጭት ለመጫርና በሙስሊሙ ላይ የተቀነባበረ የኢስላሞፎቢያ (Islamophobia) ንፋስ ለማንፈስ እንደሚፈልጉ በግልጽ ያሳየ ክስተት ነው። ይህ ጽሑፍ፣ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች በትናንትናውም ሆነ በዛሬው ሥርዓት ውስጥ ማቆሚያ ያላገኙትንና ማህበረሰቡን ዘወትር እሳት በማጥፋት ላይ ብቻ እንዲጠመድ አድርገው የተተዉትን እረፍት የነሱ የመብት ጥሰቶች፣ ጥቃቶችና ግድያዎች በዝርዝር ያሳያል። ከእነዚህም መካከል የመስጂዶች መፍረስና ቃጠሎ፣ እንደ አክሱምና ላሊበላ ባሉ አካባቢዎች መሠረታዊ የእምነት ነጻነቶችን እንኳ ማጣት፣ እንዲሁም እዚሁ አዲስ አበባን ጨምሮ እንደ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባሉ ሀገራዊ ስመ-ጥር ተቋማት ውስጥ በውስጣዊ መመሪያ የሙስሊሞች የእምነት ነጻነት ተጥሶ መቀጠሉ የዚሁ ዘላቂ መከራ ማሳያዎች ናቸው። ለቅሶን የመቀማት ስልት እና የተገላቢጦሽ ፍረጃ ⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕⭕ እነዚህና በርካታ የመብት ጥሰቶች እያሉበትም እንኳ፣ እንደ ሌላው ማህበረሰብ በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል የሚንቀሳቀስ የሙስሊሞች የተደራጀና የታጠቀ ኃይል በሌለበት ሁኔታ፤ የማህበረሰቡን የትዕግስት ልክ የሚያሳየው ይህ እውነታ ራሱ በተገላቢጦሽ ተጠቂውን ማህበረሰብ በፍረጃ ኢላማ ያደረጉ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻዎችን እያስተናገደ ይገኛል። የሚገርመው ደግሞ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻው መሪዎችና ተሳታፊዎች፤ ራሳቸው ለአብዛኛዎቹ የሙስሊሞች ጥቃቶች አቀናባሪዎችና ተዋናዮች መሆናቸው ነው። እነዚህ አካላት በኦርቶዶክስ ክርስትና ‘ሞዓ ተዋሕዶ’ እና ‘ፋኖ’ የርዕዮተ-ዓለም ጥምረትና ቁርኝት የተደራጁ፣ እንዲሁም በሃይማኖት ጥላቻ ተነሳስተው ሙስሊሞችን እያጠቁ ያሉ አካላት ደጋፊዎች ናቸው። የእነዚሁ አካላት የማህበራዊ ሚዲያ ክንፎች በተደራጀ መልኩ ከአካባቢያዊ ይዘት ወደ ሀገር አቀፍ ደረጃ ያሳደጓቸው ለጥቃት የማመቻቸት የፕሮፓጋንዳ ዘመቻዎች፤ ከዓመታት በፊት በአማራ ክልል በጥላቻ በተሞላ ቅስቀሳ ምክንያት የክልሉ ሙስሊሞች ጥቃቶችን ያስተናገዱባቸው ክስተቶች ሀገር አቀፍ ቅጂዎች ናቸው። ይህ ሁኔታ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሃይማኖት ግጭት በመፍጠር ሀገሪቱን ለማተራመስና ሕዝበ ክርስቲያኑን በሃይማኖት ጎራ በማሰለፍ ‘በዚያ ውስጥ እናተርፋለን’ ብለው ያቀዱት የተሳሳተ ዕቅድ አካል ነው። መስሏቸው ነው እንጂ በዚህ አካሄድ የኢትዮጵያ ጠላቶች ካልሆኑ በቀር ሀገሩንና ሕዝቡን የሚወድ፥ የሀገሩ ሁኔታ ግድ የሚለው ሁሉ ፈጽሞ ከሀገራችን መተራመስ የሚያተርፈው አይኖርም። የሚዲያዎችንና የፖለቲካ ልሳናትን ዘገባዎች ስንታዘብ፤ እውነታውን የማድበስበስና ‘የቅኝት ልወጣ’ (Framing) የማድረግ ስልታዊ አካሄድ በጉልህ ይታያል። አብዛኛው ተጠቂ ሙስሊም በሆነበት ክስተት ላይ-የማህበረሰቡ ሃይማኖታዊ መታወቂያ እንዲደበቅና ጥቃቱ እንዲቃለል-ብሔራቸው ብቻ እንዲጎላ ተደርጎ «አማራ ተጠቃ» ይባላል። በተቃራኒው ደግሞ የተጠቂዎቹ እምነት ክርስቲያን ሲሆን፣ ብሔራቸው ታልፎ «ኦርቶዶክስ ተገደለ» በሚል ሃይማኖታዊ መልክ እንዲይዝ ይደረጋል። ይህ የተገላቢጦሽ አካሄድ በተቋማትና በሃይማኖት መሪዎች ላይም ይደገማል፤ ታዋቂ ሼኽና ኢማም ሲጠቁ ማንነታቸውን ለመሰወርና የጥቃቱን ባህሪ ለመደበቅ ሲባል «አንድ የሃይማኖት አባት» በሚል በደፍኑ ይጠቀሳል። ቤተ-ክርስቲያን ሲጠቃ «ቤተ-ክርስቲያን ተቃጠለ/ተደፈረ» ተብሎ ቀጥተኛ ስሙ የሚጠራ ሲሆን፥ መስጂድ ሲፈርስ ወይንም ሲቃጠል ግን ስሙ ተለዝቦ «የእምነት ተቋም ተጠቃ» በሚል አጠቃላይ አገላለጽ ይሸፈናል። ይህ ሁሉ የሙስሊሙን ተበዳይነት የመሰወርና ‘የሙስሊሞችን ለቅሶ የመቀማት’ ስልት ነው። ለቅሶን መቀማት ደግሞ ተራ ነገር አይደለም፤ ልክ ታሪክን እንደ መቀማት ይቆጠራል። ታሪክና ለቅሶ ሲቀሙ፣ በአሁኑም ሆነ በቀጣዩ ትውልድ ዘንድ የማንነትና የክስተቶች ግንዛቤ መዛባት (Cognitive Distortion) እንዲፈጠር ስለሚያደርግ፣ ተበዳዩን ማህበረሰብ ድምፅ አልባ የማድረግ ዘላቂ ሂደት አካል ነው። የእነዚህ አካላት አውዳሚ አካሄድ ግን በዚህ ብቻ አልተገደበም። ይልቁኑ እጅግ ርቀው በመጓዝ፣ እውነተኛውን ተበዳይ ሕዝበ-ሙስሊም መልሶ ወደ መወንጀል ደረጃ ደርሰዋል። በደል አድራሾቹ ሰለባውን መልሰው በወንጀለኛነት የሚፈርጁት፣ የራሳቸውን ታሪካዊና መዋቅራዊ ጥቃት ለመሸፈን በሚቀይሱት ስልታዊ የፕሮፓጋንዳ ማጭበርበር ነው። ይህ የተገላቢጦሽ ፍረጃ ተበዳዩ ማህበረሰብ ለፍትህ የሚያሰማውን ድምፅ በማንኳሰስ፣ በጥቃቱ ላይ ሕጋዊና ተገቢነት ያለው አስመስሎ ለማቅረብ የሚተገበር አደገኛ የሚዲያ ዘመቻ ነው። በዚህም ምክንያት እውነተኛዎቹ ሰለባዎች ከደረሰባቸው ሁለንተናዊ መከራ በተጨማሪ፣ በዓለም ፊት ጥፋተኛ ተደርገው እንዲታዩ በመደረጉ ሁለተኛ ዙር የስነ-ልቦና እና የማንነት ጥቃት የማመቻቸት ሂደት ነው። «ስለኦርቶዶክ ዝም አንልም!» 🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸 በእርግጥ እንደ ሕዝበ-ሙስሊሙ ሁሉ፣ የኦርቶዶክስ ክርስቲያኖችም ባለፉት ዓመታት በሀገራችን የተለያዩ አካባቢዎች የጥቃት ሰለባ መሆናቸው የማይካድ ሀቅ ነው። በዚህም ምክንያት ድምፃቸውን ቢያሰሙ፣ ፍትህ ቢጠይቁና ለእምነት ወገናቸው አጋርነታቸውን ቢገልጹ ተፈጥሯዊና ተገቢ መብታቸው ነው። ሆኖም ግን፣ የኦርቶዶክስ ክርስቲያኑን መብትና ማንነት ለማስከበር የሚደረገው የፍትህ ፍለጋ ሂደት፤ ማህበረሰቡን ለማደራጀትና ለማሰባሰብ ሲባል ብቻ፣ በክስተቶቹ ውስጥ ምንም ዓይነት ሚና የሌላቸውን ሙስሊሞች ዋና ኢላማ ባደረገ መልኩ ማቅረብና ትግሉ እንዲጓዝ መጣር ፍጹም ተቀባይነት የሌለው ከጥቃቱ የከፋ ሌላ የበደል ተግባር ነው። እንበልና በተፈጸሙት የኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ጥቃቶች ጀርባ ሙስሊም የሆኑ ግለሰቦች ተሳትፈው ቢገኝ እንኳ፣ ተጠያቂነቱ ሕግን መሠረት ባደረገ መልኩ በግለሰቦቹ ላይ ብቻ ሊያርፍ ይገባል እንጂ፣ በጉዳዩ ላይ አንዳች እውቅናም ሆነ ተሳትፎ የሌለውን በሚሊዮኖች የሚቆጠርን አጠቃላይ የሙስሊም ማህበረሰብ በሚያካትት መልኩ በጥላቻ አጉልቶና ለጥጦ ማቅረብ እጅግ አደገኛ አካሄድ ነው። የጽሑፉ ዓላማ፣ መነሻዎችና የማስረጃ ምንጮች 💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢
без подписи
🐏 ኡድሒያን የሚመለከቱ ወሳኝ ነጥቦች 🔴 ኡድሒያ ማለት በዐረፋ በዓል ቀን እና ቀጥሎ ባሉ ተከታታይ ሶስት ቀናት ውስጥ ወደ አላህ ለመቃረብ ተብሎ የሚታረድ የቤት እንሥሳ ማለት ነው። "ኡድሒያ" የተባለው የእርዱ ሰዓት የሚጀምረው የዒድ ቀን ረፋድ (ዱሓ) ላይ ስለሆነ ነው። 🔴 ኡድሒያ ማረድ የዲን አካልና ተወዳጅ ተግባር መሆኑ ላይ ሁሉም ሊቃውንት ይስማማሉ፤ ብዙሃኑ ሊቃውንት ዘንድ ሱንናህ እንጂ ስለት (ነዝር) ለሌለበት ሰው ግዴታ አይደለም። አቡ ሐኒፋን ጨምሮ በርካታ ግዴታ ነው የሚል አቋም ያላቸው ሊቃውንት ስላሉና በዒድ ቀን ማረድ ልዩና ከፍ ያለ ምንዳም ስላለው አቅም ያለው ሰው ኡድሒያ ማረድ ባይተው ይመረጣል፤ 🔴 ከቤት እንስሳት (ከግመል፣ ከከብት ፣ ከበግና ፍየል) ውጪ ሌላን እንስሳ ለኡድሒያ ማረድ እንደማይቻል የፊቅህ ሊቃውንት በሙሉ (ከሐሰን ኢብኑ ሳሊሕ በስተቀር) ይስማማሉ። 🔴 ለኡድሑያ የሚታረደው እንስሳ ወንድም ይሁን ሴት ለውጥ የለውም፤ ሁለትም ጾታዎች ለኡድሒያ እንደሚሆኑ (እንደ ሚበቁ) የፊቅህ ሊቃውንት ይስማማሉ። 🔴 የዒድ ቀን ከሰላተል-ዒድ በፊትና፣ ከ 14ኛው ቀን የጸሐይ መጥለቅ በኋላ የሚታረድ እርድ ከኡድሒያ አይቆጠርም። 🔴 በመሰረቱ የኡድሑያ እንስሳ መግዣ ገንዘቡን ሰደቃ ከመስጠት ይልቅ ኡድሒያ ማረዱ በአጅር ይበልጣል። ይህም የሆነው ኡድሒያ በዕለቱ ተወዳጅና ከዒድ ሰላት ጋር የተያያዘ ዒባዳህ ስለሆነ ነው። (ኢብኑልቀይም) ነገር ግን ገንዘቡን መስጠቱ ለተቸገረ ሰው ይበልጥ የሚጠቅምበት ሁኔታዎች ላይ በላጩ ገንዘብ መስጠቱ ይሆናል። (ኢብኑ ዑሠይሚን) 🔴 ብዙሃኑ የፊቅህ ሊቃውንት ዘንድ ለኡድሒያ እርድ በላጭና ተመራጩ እንስሳ በቅደም ተከተል ግመል፣ ከዛም ከብት፣ ከዛ በግ ወይም ፍየል ነው። ይህ የሚባለው ግን ግመል ወይም ከብት አንድ አባወራ ለብቻው የሚያርድ ከሆነ ነው። ለጋራ ወይም በቅርጫ ከሆነ ግን የሚያርደው ከግመልና ከከብት ይልቅ በግ ወይም ፍየል ይሻላል። ኢማሙ ማሊክ በሁሉም ሁኔታ ላይ በላጩ በግና ፍየል፣ ከዛም ከብት፣ ከዛ ግመል ነው የሚል አቋም አላቸው። ይህ በላጩና ይበልጥ ተወዳጁን ከመግለጽ አንጻር ነው እንጂ ከ4ቱ የቤት እንስሳት ውስጥ ማንኛውንም ቢያርዱ ትክክል ይሆናል። 🔴 ለኡድሒያ የሚታረድ ማንኛውም እንስሳ ቁመናና መልኩ የሚያምረው፣ ስጋው ይበልጥ ጣፋጭና ንጹህ ይሆናል የሚባለውና በዋጋም ውድ የሆነው ከዚህ ተቃራኒ ከሁኑ እንስሳት ይልቅ ለኡድሑያ ተወዳጅ እንደሚሆን ሊቃውንት ይስማማሉ። (አን'ነወዊይ) ይህም ኡድሒያ የሚታረደው ለአላህ ተብሎ ስለሆነና ለርሱ የሚደረግ ነገር በሙሉ ንጹሁ፣ ትልቅና የሚያምር መሆን ስለሚገባው ነው። 🔴 ለኡድሒያ የሚታረድ እንስሳ እድሜው በግ ከሆነ 6 ወርና ከዛ በላይ፣ ፍየል ከሆነ 1አመትና ከዛ በላይ፣ ከብት ከሆነ 2 አመትና ከዛ በላይ፣ ግመል ከሆነ 5አመትና ከዛ በላይ መሆን አለበት። ዕድሜው እዚህ ከተጠቀሰው በታች የሆነ እንስሳ ለኡድሒያ በቂ አይሆንም። 🔴 በተፈጥሮ ምንም ቀንድ የሌለው ወይም ቀንዱ በጣም ትንሽ የሆነ፣ ጭራ ወይም ላት የሌለው፣ የተኮላሸ፣ ጆሮው የተሰነጠቀና ከግማሽ በታች የሚሆነው ብቻ የተቆረጠ እንስሳን ለኡድሒያ ማረድ ችግር የለውም። በላጩ ግን ቀንድ ያለውና አካላቱ ሙሉ የሆኑትን ማረዱ ነው። 🔴 ግልጽ የሆነና እንደልቡ ተንቀሳቅሶ እንዳይበላ የሚያደርግ ሸፋፋነት ያለበት፣ አንድ ወይም ሁለቱም አይኑ የማያይ፣ በጣም ከመክሳቱ የተነሳ ቅልጥም፣ ጮማና ሞራው ያለቀ/የሌለው፣ ግልጽ የሆነ በሽታ ወይም የበሽታ ምልክት ያለበት ማንኛውም እንስሳ ለኡድሒያ አይሆንም። ከላይ ከተጠቀሱት እንከኖች ጋር ተመሳሳይና የባሰ እንከን ያለበትንም ማረድ አይቻልም። ነገር ግን ከእነዚህ እንከኖች መካከል ቀላልና ግልጽ ያልሆነ ያለበትን ማረድ አማራጭ ካጡ እንደሚቻል ሊቃውንት ይስማማሉ።ጤነኛና ከእንከን ንጹህ ሆኖ የገዙት እንስሳ ያለጥንቃቄ ጉድለት ከላይ የተጠቀሱ እንከኖች ቢገጥሙት ማረድ ይቻላል፤ አቅም ያለው ሰው ሌላ ቢቀይር ግን ይመረጣል። 🔴 አንድ በግ ወይም ፍየል ለአንድ አባወራ እስከ ቤተሰቦቹ፣ አንድ ከበት ወይም ግመል ለ7 እና ከዛ በታች ለሆኑ አባወራዎች ( ቤተሰቦች) ይበቃል። አንድ ሰው ኡድሒያው ላይ ማንኛውንም (በህይወት ያለም ይሁን የሞተን) ሰው በምንዳው ማጋራትና ማካተት ይችላል። ለአንድ አብሮ ለሚኖር ቤተ ሰብ አንድ ኡድሒያ የሚበቃ ከመሆኑም ጋር አቅም ያለው በሙሉ በስሙ ኡድሒያ ቢያርድ መልካም ይሆናል። 🔴 አንድ እንስሳ ቤት ውስጥ ተወልዶ ያደገ (የረባ)ም ይሁን፣ እራሱ ወይም ገንዘቡ በስጦታ መልኩ የተገኘም ይሁን በማንኛውም ህጋዊ በሆነ መንገድ የራስ የተደረገ ከሆነ ለኡድሒያ ነይቶ ካረዱት በቂ ይሆናል። የግድ በጊዜው ለኡድሒያ ተብሎ በራስ ገንዘብ የተገዛ ካልሆነ አይባልም። 🔴 አንድን እንስሳ ለኡድሒያ ከወሰኑት በኋላ ሀሳብ ቀይሮ ማረዱን መተው፣ መሸጥ ወይም ለሌላ ሰው ስጦታ መስጠት አይቻልም።ግዴታ ላልሆነ ኡድሒያ የተዘጋጀ እንስሳ ያለጥንቃቄ ጉድለት ቢጠፋ ሌላ መተካት ግዴታ አይሆንም። 🔴 ለኡድሑያ የታረደን እንስሳ ቆዳውንም ይሁን ምኑንም መሸጥ፣ ለአራጅ ክፍያ ይሆን ዘንድ ብሎ ምንም ነገር መስጠት አይቻልም።በምንም መልኩ ክፍያው ላይ ተጽዕኖ ሳይኖረው ለአራጅ እንደተጨማሪ ስጦታ ወይም ሰደቃ መስጠት ግን ይቻላል። ኡስታዝ አሕመድ አደም
🛑 የአረፋ ቀን ፆም! ነቢዩ (ﷺ) ስለ አረፋ ቀን ፆም ተጠይቀው እንዲህ ብለዋል፦ “ያለፈውንና የመጪውን አመት ወንጀል ያስምራል።” 📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 1162 🛑 የአረፋ ቀን ፆም የሚፆመው ነገ ማክሰኞ ግንቦት 18 ነው ⚫️ ቀዳ ያለበትም ሰው ቢሆን የዐረፋን ቀን ጾም መጾም ይችላል። ⚫️ ማንኛውም ከነጋ በኋላ ምግብና መጠጥ ያልቀመሰ ሰው ከነጋ በኋላም ቢሆን ነይቶ ጾም መጀመር ይችላል። ነገር ግን ምንዳው የሚጀምረው ከነየተበት ሰዓት ጀምሮ ነው። ⚫️ከ9ኛው ቀን በፊት ምንም ላልጾመ ሰውም ቢሆን 9ኛው ቀን ብቻ መፆም ይቻላል/ችግር የለውም። ⚫️በዐረፋ (9ኛው ቀን) ላይ ይበልጥ የሚወደዱ 3 ዒባዳዎች፣ 1/ ቀኑን መጾም 2/ ዚክር ማብዛት በተለይም ተክቢር 3/ ዱዓእ ማብዛት ⚫️ለዐረፋ ቀን ራሱን የቻለ ዱዓእ የለውም ሁሉም የቻለውንና የሚፈልገውን ዱዓእ ማድረግ ይችላል። 🛑 የአረፋ ቀን ፆም የሚፆመው ነገ ማክሰኞ ግንቦት 18 ነው
ሆኖም ዛሬ ደቡብ አፍሪካ ያሳለፈችውን የመከራ ታሪክ ባለመርሳትና ለጊዜያዊ ጥቅም ባለመታለል ዋጋ በመክፈል ጭምር በእስራኤል ላይ በዓለም አቀፉ ፍርድ ቤት የጀመረችውን የዘር ማጥፋት (Genocide) ክስ ኢትዮጵያ መቀላቀል ቢያቅታት እንኳ በጄኔቫው መድረክ ድጋፍ መስጠት አለመቻሏ ፣ ያንን ታላቅ የፓን አፍሪካዊነት መሪነትና ለተገፉ ወገኖች የመቆም የታሪክ ባለቤትነት የሚያሳንስ እጅግ አሳዛኝ ክስተት ሆኖ አግኝቼዋለሁ። የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየምን የመሰለ ታላቅ የነፃነት ምልክት ያስገነባ መሪ፣ በሊግ ኦፍ ኔሽንስ መድረክ ለፍትህ የተሟገተች ሀገርን የሚመራና ከመሬቴ አታፈናቅሉኝ በሚል ተቃውሞ መነሻነት በመጣ ለውጥ ወደ ሥልጣን የመጣ መሪ፤ በየትኛውም የዓለም ክፍል የሚፈጸምን የመሬት ነጠቃ፣የማፈናቀልና የመሬት ወረራ የመቃወም ታሪካዊና ሞራላዊ ግዴታ አለበት ብዬ አምናለሁ። ስለሆነም፣ ኢትዮጵያ ከነጃሺ ዘመን ጀምሮ ለተገፉ ወገኖች ከለላና አጋር የመሆን፣ የእውነት ድምፅ ሆኖ የመቆምና የፍትህ ፋና ወጊነት ታሪኳን በዓለም መድረክ እንድትቀጥል፤ አስተዳደርዎ የወሰደውን ይህንን አቋም በድጋሚ እንዲመረምረውና አስፈላጊውን የታሪክ እርምት እንዲያደርግ በታላቅ አክብሮትና በዜግነት ኩራት እጠይቃለሁ። አሕመዲን ጀበል
ይህንን አቤቱታ በግንባር ቀደምትነት የመሩት ሊቀመንበሩ ኤርዊን ክራፍት (Erwin Kraft)፣ ዋና አራማጁ ኸርማን ፉርንበርግ (Hermann Fuernberg) እና ማሪ ጊንስበርግ (Marie Ginsberg) ሲሆኑ፣ ጥያቄያቸውን ለማስፈጸም እንደ ጆን ደብሊው ፔህሌ (John W. Pehle) ካሉ የአሜሪካ የጦርነት ስደተኞች ቦርድ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር የቅርብ ግንኙነት ነበራቸው። በቀረበው ዕቅድ መሠረት ከ60,000 እስከ 70,000 ስኩዌር ማይል የሚሸፍን ሰፊ የሐረርጌ መሬት ለአይሁድ ሰፋሪዎች እንዲሰጥና ግዛቱ የራሱ ሕገ-መንግሥትና በእንግሊዝኛ የሚመራ አስተዳደር እንዲኖረው የሚጠይቅ ነበር። ይህ የሰፈራ ዕቅድ ሐረርጌን ለኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ሉዓላዊነት በስም አስገዝቶ፣ በውስጥ ግን በሕዝብ በሚመረጥ ምክር ቤት የምትመራና በብሪቲሽ ሶማሊላንድ በኩል በበርበራና ዘይላ ወደቦች የባሕር መውጫ እንዲኖራት የታቀደ ራስ-ገዝ ግዛት ለመመሥረት ያለመ ነበር። ሐረርጌ ለዚህ ፕሮጀክት የተመረጠችው የአየር ንብረቷ ለአውሮፓውያን ሰፋሪዎች ምቹ በመሆኑ፣ ምድሪቱ "ሰው ያልሰፈረባት" (sparsely populated) ናት ተብሎ በመታመኑና በዞሀር (Zohar) መጽሐፍ "የአይሁድ ስደት በኩሽ ምድር ያበቃል" ተብሎ ስለተጻፈ ሲሆን፣ ዕቅዱን ያቀረቡት ወገኖችም ንጉሠ ነገሥቱ የአሁድ ዘር ነኝ(ዘእምነ ነገደ ይሁዳ) ይኑ ስለነበር ለአይሁድ ሰፋሪዎቹ በጎ አመለካከት ይኖራቸዋል የሚል ጽኑ እምነት ነበራቸው። በተጨማሪም ግዛቱ ለእህል፣ ለፍራፍሬና ለአትክልት ምርቶች አመቺ መሆኑ ተጠቅሶ፣ እያንዳንዱ ሰፋሪ ለንጉሠ ነገሥቱ ታማኝነት እንዲምልና ግዛቱ የተወሰነ የግብር ድርሻ እንዲከፍል ሐሳብ ቀርቦ ነበር። የኢትዮጵያ መንግሥት እ.አ.አ. በሐምሌ 4 ቀን 1944 በሰጠው ይፋዊ ምላሽ ይህንን ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ውድቅ በማድረግ የሐረርጌን ሕዝብ ከታላቅ የታሪክ አደጋ ታድጓል። የአጼ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት ምላሽ ሲሰጥ፣ ሀገሪቱ በጣሊያን ወረራና ውድመት ምክንያት በሺዎች የሚቆጠሩ የገዛ ዜጎቿ መጠለያ አጥተው ባለበት ሁኔታ፣ አንድን ሙሉ ጠቅላይ ግዛት ለስደተኛ ቡድን አሳልፎ መስጠት የሀገሪቱን ኢኮኖሚ አደጋ ላይ የሚጥልና የማይቻል ተግባር እንደሆነ በግልጽ አስታውቋል። ንጉሠ ነገሥቱም ፕሮጀክቱና ለፕሮጀክቱ የተሰጠው ስያሜ ጭምር ሙሉ በሙሉ እንዲተውና እንዲቆም ጥብቅ ትእዛዝ ማስተላለፋቸው፣ ዛሬ በሐረርጌ ምድር ላይ ሊከሰት ይችል የነበረውን መጠነ-ሰፊ መፈናቀል፣ የዘር ፍጅትና የማንነት መጥፋት አደጋ የቀለበሰ ታላቅ ብሔራዊ ውሳኔ ሆኖ በታሪክ ተመዝግቧል። ይህ በሆነ ከአራት ዓመታት በኋላ የፍልስጤም ምድር በወረራ ተይዞ እ አ አ በ1948 የአይሁድ ግዛት በመሬታቸው ላይ ተመሰረተ። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ፊሊስጤሞች በገዛ ሀገራቸው መሬታቸው የመሬት ወረራ፥ መፈናቀልና ግድያ እያስተገዱ ይገኛሉ። ዛሬ በፍልስጤም ምድር ላይ የሚታየውን የሰፈራ ወረራና የዘር ማጥፋት ድርጊት ያ የሰፈራ ዕቅድ በወቅቱ ውድቅ ባይደረግ ኖሮ፣ ዛሬ በጋዛና በዌስት ባንክ በፍልስጤማውን ላይ የሚፈጸመው ጭፍጨፋ በሐረርጌ ኦሮሞ አርሶ አደሮች፥ በሱማሌና ሌሎች ኢትዮጵያውያን ላይ አየተፈጸመ ይገኝ ነበር። ፍልስጤማውያን በነጻነት እየነሮ ሰቆቃው የእኛ የኢትዮጵያውያን እጣ ፈንታ፣ የሰሞኑን በጄኔቫ የተካሄደው ስብሰባ በቀጥታ ስለ እኛ ይሆን ነበር። በመሆኑም በጄኔቫው ጉባዔ ላይ ሀገራችን የሰፈራ ግንባታን የሚቃወመውን ውሳኔ "አይ" (No) ስትል፣ በታሪክ መነፅር ግን የገዛ መሬታችን የሆነችውን ሐረርጌን ለባዕድ ወረራ አሳልፎ ለመስጠት የሚደረግን ጥረት "አልቃወምም" እንደማለት ይቆጠራል። የገዛ መሬታችን በባዕዳን ሲወረርና ሕዝባችን ሲፈናቀል ሌሎች ሀገራት በዝምታ ቢያልፉት የሚሰማንን ስሜት ማሰብ፣ ዛሬ ለወሰድነው አቋም ትልቅ የታሪክ እርምትና የሞራል ማነጻጸሪያ ሊሆነን ይገባል። የ"አባ ለፉማ" እሴት እና የጄኔቫው ድምፅ አሰጣጥ የታሪክ እርምት ጥሪ ♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦♦ ክቡር ጠቅላይ ሚ/ር እርስዎን ወደ አመራርነት ያመጣዎት ታሪካዊ ለውጥ መሠረቱ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የመብት ንቅናቄ (ድምፃችን ይሰማ) ተጀምሮ፣ ለዓመታት ዘልቆ ተቃውሞ የበረታበት የኢህአዴግ መንግስት በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን በሚል የነደፈው እቅድ በአዲስ አበባ ዙሪያ የሚኖሩ የኦሮሞ ገበሬዎችን ከገዛ መሬታቸው ያፈናቅላል በሚል በተነሳው የኦሮሞ ተቃውሞ (Oromo Protest) ነበር። የኦሮሞ ወጣቶች “Lafti keenya lafee keenya!” (መሬታችን አጥንታችን ነው!) በሚል መሪ ቃል በጽኑ በመቃወማቸው የተቀጣጠለው ተቃውሞ ወደ ሌሎች አከባዎች ተስፍቶ በሀገራችን የመንግሥት ለውጥ እንዲመጣ ምክንያት ሆኗል። በመሆኑም በማስተር ፕላን ስም የመሬት ወረራ ሊደረግ ነው በሚል ተቃውሞ መነሻነት በፈነዳ ሕዝባዊ ተቃውሞ ወደ ሥልጣን የመጣ መሪ፣ ዛሬ በሌላ ሕዝብ መሬት ላይ የሚፈጸመውን የሰፈራ ወረራ በጄኔቫ መድረክ "ተቃውሞን አለማሳየት" እጅግ የሚቆረቁር የታሪክ ተቃርኖ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። እርስዎ ከኦሮሞ ማህበረሰብ የወጡ መሪ እንደመሆንዎ፣ የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ በኦሮሞ ሕዝብ ያለውን የ"አባ ለፉማ" (Abbaa lafummaa)/ የመሬት ባለቤትነት ክብርና የሞት ሽረት ትግል ጠንቅቀው ያውቃሉ። በሌሎች መሬት ላይ የሰፈራ ግንባታ ማለት ቀጥተኛ የመሬት ነጠቃና ማንነትን የማጥፋት ሂደት በመሆኑ፣ የመሬት ባለቤትነት መብታችን ተከብሮና ማንነታችን ጸንቶ እንድንኖር የተደረገው ትግል በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ለተገፉ ወገኖች ድምፅ እንድንሆን የሚያስገድደን የ"አባ ለፉማ"(Abbaa lafummaa)/ የመሬት ባለቤትነት ታሪክ ቃል-ኪዳን ሊሆነን ይገባል። ማጠቃለያ 🎒🎒🎒🎒 ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ሆይ፤ በዚህ ውስብስብ ጂኦ-ፖለቲካዊና ወቅታዊ የዓለም አቀፍ ሁኔታ ውስጥ ሀገርን በጥበብ መምራት፥ ጥቅሟን ማስጠበቅ እና በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ እሴትን ያማከለ እና ጥቅምን የራስን ጥቅም ሚዛን የጠበቀ ጽኑ አቋም መያዝ ከፍተኛ ጥንቃቄን የሚጠይቅ መሆኑን አረዳለሁ። በአስተዳደርዎ ላይ ልዩ ልዩ ዲፕሎማሲያዊ ጫናዎች ቢኖሩ እንኳ ከአፍሪካ ሕብረት የቆየና የጸና አቋም ጋር ፍጹም የሚቃረንና ወደ ጽንፍ የሄደ፥ ከብዙሃን በተራቃኒ ሀገሬን ከቼክ ሪፐብሊክና ከሰሜን ሜቀዶኒያ ጋር ብቻ በመቆም የ"ተቃውሞ" (No) ውስጥ መግባት ግን እጅግ አሳዛኝ የታሪክ ክስተት ነው። ቢያንስ ቢያንስ እንደው በማናውቀው ምክንያት በዚያ ሰሞን በይፋ መደገፉ መዘዙ ቢያይል እንኳ ለጊዜው በድምፅ አሰጣጡ ላይ "ድምፀ ተዓቅቦ" (Abstain) ማድረግ ወይም በስብሰባው ላይ ባለመገኘት ዲፕሎማሲያዊ ሚዛኑን መጠበቅ ይቻል ነበር፤ ሆኖም አሁን የታየው ከድጋፍና ከአጋርነት ወደ ግልጽ ተቃውሞ የተደረገው ሽግግር፣ ሀገራችን ለዘመናት ለተገፉ ወገኖች የነበራትን የሞራል መሪነት ዋጋ ያሳነሰና እጅግ የሚቆረቁር ውሳኔ ነው። ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ሆይ፤ 🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 ኢትዮጵያ በአፓርታይድ ትግል ወቅት ለኔልሰን ማንዴላ የወታደራዊ ስልጠና በመስጠት፣ የኢትዮጵያ የጉዞ ፓስፖርትና የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ለደቡብ አፍሪካ ነፃነት የነበራት ግንባር ቀደም ሚና የሀገራችን የታሪክ ኩራት ነው።
የሐረርጌው የዘር ፍጅትና የጄኔቫው ተቃውሞ 💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥 ከአሕመዲን ጀበል 🔴🔴🔴🔴🔴🔴 ይድረስ ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) 💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢 ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፤ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረክ ያላት ክብር የሚመነጨው ለዘመናት ካካበተችው የነፃነት ታሪክ እና ለፍትህ ከምትሰጠው ጽኑ ድምፅ እንደሆነ አምናለሁ። ሆኖም በቅርቡ በጄኔቫ በተካሄደው 61ኛው የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት (UNHRC) መደበኛ ስብሰባ ላይ፣ በእስራኤል ሕገ-ወጥ የሰፈራ ግንባታና በወረራ በተያዙ የፍልስጤም ግዛቶች ላይ የሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን የሚኮንነው የውሳኔ ሐሳብ (Resolution A/HRC/61/L.36) ቀርቦ ነበር። በዚህ ታሪካዊ መድረክ ላይ 34 ሀገራት ለፍትህና ለዓለም አቀፍ ሕግ የበላይነት ድምፃቸውን ሲሰጡ፣ የእርስዎ አስተዳደር ግን ይህንን የሰፈራ ግንባታ የሚቃወመውን ውሳኔ ባለመደገፍ "አልቃወምም" (No) የሚል ድምፅ መርጧል። ይህ በኢትዮጵያ ስም የተሰጠው ድምፅ ከሀገራችን ታሪካዊ ስነ-ልቦና፣ ከዲፕሎማሲያዊ እሴቶቻችን እና ከገዛ ሕዝባችን ቀኝ አልገዛም በሚል ሲፋለም ካሳለፋቸው የመከራ ጋር ፍጹም የሚጋጭ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። ስለሆነም፣ ይህንን ውሳኔ በሚከተሉት ታሪካዊ፣ ሞራላዊና ፖለቲካዊ መሠረቶች ላይ ተመርኩዤ እንደ አንድ ዜጋ እንዲታረም በታላቅ አክብሮት መጠየቅ እወዳለሁ። የአድዋ ውርስ፣ የመታሰቢያ ሙዚየሙ ኩራትና የጄኔቫው ድምፅ አሰጣጥ የታሪክ ተቃርኖ ✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅ የኢትዮጵያዊ ማንነታችንን ካጸኑ መሠረቶች አንዱ በአድዋ ፍልሚያ ሜዳ የጸናው 'ለእውነት መቆም' እና 'ወረራን በጽኑ መቃወም' የሚለው የቆየ እሴታችን እንደሆነ አምናለሁ። ይህ በ1896 አባቶቻችን ያስመዘገቡት የአድዋ ድል ለእኔ የአንድ ሀገር ስኬት ብቻ ሳይሆን፣ የመላው ጥቁር ሕዝቦችና በዓለም ዙሪያ የሚገኙ የተገፉ ወገኖች ሁሉ የነፃነት ፋና እንደሆነ ይሰማኛል። አዲስ አበባም የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ እንድትሆን የተመረጠችው በአድዋ ላይ ከቀኝ ገዢዋ ጣሊያን ጋር በመፋለም ለነጻነቷ ባስመዘገበችው አነቃቂ ድልና ለሌሎች ሕዝቦች ለነፃነትና ለፍትህ ባላት ጽኑ አቋም መሆኑን ጠንቅቄ አውቃለሁ፤ ሆኖም በጄኔቫው የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ጉባዔ ላይ፣ በእስራኤል የሰፈራ ግንባታ ላይ የቀረበውንና ድርጊቱ በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት ሕገ-ወጥ መሆኑን የሚያረጋግጠውን የውሳኔ ሃሳብ ሀገሬ ለመደገፍ ፈቃደኛ አለመሆኗ እጅግ አሳዝኖኛል። የአድዋ ድልን ለማሰብና የጀግኖች አባቶቻችንን ገድል በትውልዱ ለማስረጽ ተምሳሌትነትን ለማጉላት የአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም በእርስዎ መሪነት በአዲስ አበባ እምብርት ፒያሳ ላይ "የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም" መገንባትና ለነጻነት ትግል ከፍያለ ስፈራ መሰጠቱ እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ በአዎንታዊ ጎኑ ከሚያዩነት ነኝ። በተለይ «አድዋ ዜሮ ዜሮ» የሚል ስያሜ መያዙ ደግሞ የርቀት መለኪያ ጅማሮ ስፍራ ለሀገራችን እና ለህዝችን ነጻነት በጋራ ዋጋ የተከፈለበት ስፍራ መሆኑ ልዩ ትርገም አለው። ይህ ግዙፍ ማዕከል የጀግኖች አርበኞች ታሪክ በዘመናዊ መንገድ የሚዘክር የኪነ-ሕንጻ ጥበብ ውጤት በመሆኑ እጅግ ደስ የሚያሰኝ ነው። በተለይም ልዩ ልዩ የዓለም ሀገራት መሪዎችና ከፍተኛ ልዑካን ይህንን ማዕከል ሲጎበኙ ስመለከት፣ የአድዋን ትርጉም ለዓለም በማሳወቅዎና የድል ታሪካችንን በክብር ለማስተዋወቅዎ እንደ ዜጋ ታላቅ የባለቤትነት ስሜት ይሰማኛል። ይህ ሙዚየም ለኔ ለነጻነታችንን ዋጋ ለመፈክል ወደ ኋላ የማይል ማንነት እንዳለን በድንጋይ ላይ የታተመበት እና ለዓለም ሁሉ ድምፃችንን ከፍ አድርገን የምናሳይበት ታላቅ መድረክ ነው። እንዲህ ያለውን ታላቅ ማዕከል ያስገነባ መሪ የአድዋ ድልን መሠረታዊ ትርጉም ከማንም በላይ ይገነዘባል ብዬ እገምታለሁ። ሆኖም ግን፣ በጄኔቫው ድምፅ አሰጣጥ የታየው አቋም ግን ካገኘሁት ብሔራዊ ኩራት ጋር የሚጋጭ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። ለእኔ የአድዋ ትርጉም "መሬቴን አላስካም፤ ነፃነቴንም አላስደፍም" የሚል ጽኑ የሉዓላዊነት እና የፍትህ መልዕክት ነው። በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ የፍልስጤም ህዝብ የዘር ማጽዳት እየተካሄደበት በሚገኝበት የታሪክ ወቅት ላይ መሬቱን በሰፈራ የመንጠቅ ተግባር በሚወገዝበት መድረክ ሀገሬ ተቃውሞን አለማሳየቷ፣ ካስገነቡት የአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም መንፈስ ጋር ፍጹም የሚቃረን ሆኖ ይታየኛል። 34 ሀገራት ለፍትህ ድጋፋቸውን ሲሰጡ፣ ሀገሬ ከሁለት ሀገራት ጋር ብቻ ተነጥላ በወረራ ተግባር ላይ ተቃውሞዋን አለመግለጿ፣ የተገነባውን ታሪካዊ ስም የሚሸረሽርና ኢትዮጵያ ለዘመናት ለተገፉ ወገኖች የነበራትን የሞራል መሪነት ዋጋ የሚያሳጣ የታሪክ ግድፈት እንደሆነ ይሰማኛል። ሊግ ኦፍ ኔሽንስ የጋራ ደህንነት መርህ እና የጄኔቫው ድምፅ አሰጣጥ ተቃርኖ 📮📮📮📮📮📮📮📮📮📮📮📮📮 ኢትዮጵያ በ1935 በፋሺስት ኢጣልያ ወረራ ሲፈጸምባትና ሉዓላዊነቷ በኃይል ሲደፈር፣ በሊግ ኦፍ ኔሽንስ መድረክ በመገኘት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ያቀረበችው የፍትህ ጥያቄ የሀገራችን የዲፕሎማሲ ታላቅ መሠረት እንደሆነ አምናለሁ። በወቅቱ ንጉሠ ነገሥቱ 'ዛሬ በእኛ ላይ የደረሰው ነገ በእናንተ ላይ ይደርሳል' በማለት ያስጠነቀቁበት የ'ጋራ ደህንነት' (Collective Security) መርህ፣ ማንኛውንም ዓይነት ወረራንና የመሬት ነጠቃን በጽኑ የሚቃወም ነበር። ሆኖም በጄኔቫው የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ስብሰባ ላይ በፍልስጤም ምድር የሚፈጸመውን ሕገ-ወጥ የሰፈራ ግንባታና ወረራ ለመቃወም ፈቃደኛ አለመሆን ግን፣ ሀገራችን በፋሺስት ወረራ ወቅት የተሟገተችለትን ታሪካዊ እሴትና የሉዓላዊነት መርህ የሚንድ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። ይህንን የውሳኔ ሐሳብ ለመደገፍ ፈቃደኛ አለመሆን፣ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ፊት ቀርበው ፋሺስት ኢጣልያ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የፈጸመውን ግፍና ወረራ ሲያጋልጡ የነበረውን የሞራል ልዕልና የሚቃረንና ሀገራችን ለዘመናት ለፍትህ የነበራትን ጽኑ አቋም የሚሸረሽር ነው። በወቅቱ ኢትዮጵያ የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በወራሪዎች ላይ እርምጃ እንዲወስድና ለተገፉ ወገኖች እንዲቆም ስትሟገት የነበረው ያ የሞራል መሠረት፣ ዛሬ በተመሳሳይ ሁኔታ ውስጥ ለሚገኝ የፍልስጤም ሕዝብ የእውነት ድምፅ እንድንሆን ታሪክ ያስገድደናል። ከሐረርጌ እስከ ጋዛ፡ የአይሁድ ሰፈራ ዕቅድ 🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 የአይሁድ ሀገር ለመመስረት ታጭተው ከነበሩት ስፍራዎች መካከል አንዷ የኛዋ ሐረርጌ ነበረች። ይህ እቅድ እውን ሆኖ ቢሆን ኖሮ ዛሬ በፍልስጤም ምድር ላይ የምናየው የመሬት ወረራ፣ የሰፈራ፥ የመፈናቀልና የጅምላ ፍጅት ሂደት በኛው ሀገር በሀረርጌና አከባቢው ይሆን ነበር። ታሪኩ እንዲህ ነበር። እ.አ.አ. በጥር 26 ቀን 1944 "የሐረር ምክር ቤት" (Harrar Council) በሚል ስያሜ በኒው ዮርክ ከተማ የተደራጁ ከአውሮፓ የመጡ አይሁዳውያን በሐረርጌ ጠቅላይ ግዛት ውስጥ ራስ-ገዝ የሆነ የአይሁድ ግዛት ለመመሥረት ለንጉሠ ነገሥቱ መንግስት ጥያቄ አቅርበው ነበር።