- Последний пост
- 25 июл.
- Последнее чтение
- 13 авг.
- Постов за неделю
- 0
- Всего постов
- 83
- Тип
- открытый
- Язык
- und
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 2 395
- 1/48двое суток
- 2 744
- 1/72трое суток
- 2 960
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
የድህረ ምርቃ መግቢያ ፈተና(NGAT exam) ምዝገባ ጊዜ ተገልጿል የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በ2018 ዓ.ም የሚሰጠውን መደበኛ የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና /National Graduate Admission Test/ ለመስጠት በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ፈተናውን ለመውሰድ እየተጠባበቃችሁ ላላችሁ የድህረ ምረቃ ትምህርት አመልካቾች በሙሉ ምዝገባ የሚካሄደው ከሀምሌ 15 – 25/2018 ዓ.ም ብቻ መሆኑን አውቃችሁ ከታች በተቀመጠው የመመዝገቢያ ሊንክ ገብታችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ለፈተናውም አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን። የፈተና መስጫ ጊዜው ወደፊት የሚገለጽ ይሆናል፡፡ የመመዝገቢያ ሊንክ፡- https://ngat.ethernet.edu.et ማሳሰቢያ:- ፈተናውን ለመውሰድ የፋይዳ መታወቂያ እንደ ቅድመ ሁኔታ መቀመጡን አውቃችሁ ከወዲሁ እንድትዘጋጁ። የአገልግሎት ክፍያ 750 ብር (ሰባት መቶ ሀምሳ ብር) መሆኑን አውቃችሁ በቴሌ ብር በኩል በምዝገባው ወቅት የሚፈጸም ይሆናል። ምዝገባው የሚከናወነው በሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ሲሆን የፈተና ጣቢያውን በሚመለከት ግን ከምዝገባ በኋላ የተመዝጋቢ ቁጥሩ ታይቶ በስታንዳርዱ መሰረት የሚወሰን ይሆናል፡፡ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት share ይደረግ @dbuinfocenter12 @dbuinfocenter12 @dbuinfocenter12
без подписи
🇪🇸Spain 🔥🔥🔥🔥🔥 deserved!
ለሁሉም የክረምት ተማሪዎች የጥሪ ማስታወቂያ !! @dbuinfocenter12 @dbuinfocenter12 @dbuinfocenter12
የደብረ ብርሃን 20ኛ ዙር ተመሪቂ ተማሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ። 🎆🎆🎉🎉🎉Congratulations @dbuinfocenter12 @dbuinfocenter12 @dbuinfocenter12
без подписи
без подписи
без подписи
✅ Do you Need Professional Graphics Design Service? 🔴Services we provide👇👇👇 ◈Professional "CV" design for job ◈ Application Letter Writing ◈ photo editing and design ◈ posture design and also ◈Banner design ◈Social media Poster design If you need #CV designer and Photo editor you can contact Me ☎️ 0972727467 // 0708043909 ▷inbox:- @Tk_Design12 ✅Tk design & Editing !!! ከ DBU info Center እንደመጡ ሲናገሩ ልዩ ቅናሽ ተዘጋጅቷል! @dbuinfocenter12 @dbuinfocenter12 @dbuinfocenter12
“በቻይና የጋብቻ ገበያ ተቋቋመ”‼️ በቻይና ሻንጋይ በሚገኝ አንድ የሕዝብ ፓርክ ውስጥ ወላጆች ለልጆቻቸው የትዳር አጋር የሚፈልጉበት ልዩ “የጋብቻ ገበያ” በየሳምንቱ መጨረሻ እየተካሄደ መሆኑን ቢቢሲ (BBC) እና ሲኤንኤን (CNN) የዜና ምንጮች ዘግበዋል። ወላጆች የልጆቻቸውን ዕድሜ፣ ቁመት፣ የትምህርት ደረጃ፣ ገቢ እና የቤት ባለቤትነት ዝርዝር መረጃ በወረቀት ላይ በመጻፍ በጃንጥላዎች ወይም በገመዶች ላይ ይሰቅላሉ። ገበያውን በብዛት የሚያደምቁት በትዳር ዕድሜ ላይ ለደረሱ ነገር ግን በሥራ መብዛት ወይም በሌላ ምክንያት አጋር ላላገኙ ልጆቻቸው የሚጨነቁ ወላጆች ናቸው። በገበያው ውስጥ ከፍቅራዊ ስሜት ይልቅ የኢኮኖሚ አቅም፣ የትምህርት ደረጃና ማኅበራዊ መደብ ለትዳር መሠረት ተደርገው በሰፊው ይገመገማሉ። @dbuinfocenter12 @dbuinfocenter12 @dbuinfocenter12
ውጤትዎን ይመልከቱ! ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም የተሰጠው የ2018 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጤት መታየት ጀምሯል። ውጤትዎን ለማየት 👇 https://result.ethernet.edu.et ሊንኩን ከተጫኑ በኋላ 'Exit Examination' ላይ 'View Results' የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤትዎን ይመልከቱ። @dbuinfocenter12
без подписи
የ 2018 ዓ.ም 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ፕሮግራም! @dbuinfocenter12 @dbuinfocenter12 @dbuinfocenter12
#inbox Debre berhan university ዩኒቨርሲቲያችን ለሰኔ 2018 exit ተፈታኞች ያሳየው ቸልተኝነት እና በጀነሬተር መፈተን ሲገባው የተፈፀመው ሀላፊነት የጎደለው ተግባር እና ስግብግብነት : አርብ ቀን 05/10/2018 የጠዋት ፈረቃ management department ስንፈተን 27 ደቂቃ ሲቀረን መብራት ጠፋ እስኪመጣ ጠብቀን ድጋሚ login ብለን ጥያቄውን ለመክፈት ስንሞክር..."you are trying to connect with another device or another browser..." የሚል warning አሳይየን ድጋሚ መግባት አልቻልንም እናም ደቂቃው ሲያልቅ በራሱ submit አለው በተመሳሳይ ዛሬም በ12/10/2018 ከሰአት ተፈታኞች 50ደቂቃ ሲቀራቸው መብራት ጠፋ ተመሳሳይ ችግር ገጠማቸው እና የተማሪዎች ውጤት ቢበላሽ እና ለባከነው ሰአት ማነው ሀላፊነቱን የሚወስደው ?? መላ በሉን መፍትሄውስ ምንድነው ?? **** ይህ በፍጹም መሆን የሌለበት ሀላፊነት የጎደለው ተግባር ነው! የሚመለከታችሁ አካላት በስህተት እንኳን አንድዬ ስህተት ቢፈጠር መደገም ግን አልነበረበትም! @dbuinfocenter12 @dbuinfocenter12 @dbuinfocenter12
ውድ ተመራቂዎቻችን እንኳን ደስ አላችሁ የምርቃት ቀን ሰኔ 21 ቀን ሆኗል 🙏 @dbuinfocenter12 @dbuinfocenter12 @dbuinfocenter12
без подписи
ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ 2 ለ 0 በማሸነፍ የዋንጫው ባለቤት ሆነ! በደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ከከተማው እግርኳስ ፌዴሬሽን ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የማስ ስፖርት (Mass Sport) የእግር ኳስ ውድድር ፍጻሜውን አግኝቷል። ዛሬ በአፄ ዘርዓያዕቆብ ስታዲየም በተደረገው ተጠባቂ የፋይናል ጨዋታ የደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ እና የፊቤላ (Phibela) ቡድኖች ብርቱና አዝናኝ ፉክክር አድርገዋል። ጨዋታው በደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ 2 ለ 0 አሸናፊነት የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ የውድድሩ የዋንጫ ባለቤት መሆን ችሏል። ይህ ንቅናቄ በከተማዋ ስፖርታዊ ባህልን ለማሳደግ፣ ጤናማ ማህበረሰብን ለመፍጠርና በተቋማት መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር ትልቅ ሚና አበርክቷል። ለተሳታፊዎችና ለደጋፊዎች በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ! @dbuinfocenter12 @dbuinfocenter12 @dbuinfocenter12
🔔 የመውጫ ፈተና ተፈታኝ ነዎት? መረጃዎችዎን አረጋግጠዋል? ከሰኔ 04-12/2018 ዓ.ም የሚሰጠውን የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ ተማሪዎች በአስቸኳይ መረጃቸውን እንዲያረጋግጡ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል። የማረጋገጥ ሥራው (Self Verification) ከ2-3 ደቂቃዎች ብቻ የሚወስድና የተፈታኞችን የትምህርት ሰነዶች ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ለማስተሳሰር የሚያስችል ነው። በመሆኑም #ለመጀመሪያ_ጊዜ የመውጫ ፈተና የምትወስዱ ተፈታኞች የFAN ቁጥራችሁን በመጠቀምና የግል መረጃ በማሟላት የራሳችሁን መለያ ማረጋገጫ ማጠናቀቅ ይጠበቅባችኋል። https://verify.ethernet.edu.et/ ላይ ይግቡ፣ Exit Examination የሚለውን ይጫኑ፣ Continue Verification የሚለውን በመጫንና የሚያስፈልገውን በመሙላት ያረጋግጡ።
💔 ዛሬ ያጋጠመን ሽንፈት ያማል፣ ልብም ይሰብራል። የእግር ኳስ ውበትና ጭካኔው የሚገለጠው በትክክል እንዲህ ባሉ ቀናት ነው። ቡድናችን እስከ መጨረሻው ሰከንድ ድረስ የታገለው ትግል፣ ተጫዋቾቹ በሜዳ ላይ ያፈሰሱት ላብ እና እኛ ደጋፊዎች ያሳየነው ፍቅር በቀላሉ የሚረሳ አይደለም። ሽንፈት የአንድ ጉዞ ማብቂያ ሳይሆን፣ ይበልጥ ጠንክሮ ለመመለስ የሚደረግ የዝግጅት ምዕራፍ ነው። አርሰናል ታሪክ ያለው፣ በውድቀት ውስጥ የማይቀር እና ሁልጊዜም እንደ ፊኒክስ ወፍ ከአመድ ላይ ተነስቶ የመብረር ብቃት ያለው ታላቅ ክለብ ነው። ኳስ ላይ ትላንት አልፏል ፣ ዛሬ ትምህርት ነው ፣ ነገ ግን አዲስ እድል ይዞ ይመጣል። ታላላቅ ስኬቶች ከመምጣታቸው በፊት እንዲህ ያሉ መራራ ሽንፈቶች መኖራቸው የማይቀር ነው።አሁንም ቢሆን የወደፊት ተስፋችን ከሌሎች እጅግ የተሻለ ነው ። ቡድኑ ካለፉት ስህተቶቹ ተምሮ በሚቀጥለው ጨዋታ ይበልጥ ጠንክሮ እንደሚመለስ አንጠራጠርም። ሲያሸንፍ አብሮ መጮህ ቀላል ነው፤ እውነተኛ ደጋፊነት ግን ቡድን ሲወድቅ ደግፎ ማነሳሳት፣ ሲሸነፍም አብሮ መቆም ነው። ስለዚህ ጭንቅላታችሁን ቀና አድርጉ! ቀይ እና ነጭ ቀለማችሁን በኩራት ልበሱ። መድፈኞች መቼም ቢሆን ብቻቸውን አይጓዙም። ዛሬ ባዝንም ነገ ግን የተሻለ ቀን እንደሚመጣ እናምናለን። የዛሬ ሳምንት እልል ያለ የ22 አመት ናፍቆት ደስታ ላይ መሆናችንንም መርሳት የለብንም !! በጣም ደስተኛ የሆኑት የ psg ደጋፊዎች ሳይሆኑ የአርሰናል ጠላቶች ናቸው, ለፍፃሜ መድረስ ሳይሆን ወደፊት መሳተፍ ብርቅ የሆነባቸው ሻሼዎች 😡🤬 Arsenal forever Whatever the weather ❤ ©DBU info Center @dbuinfocenter12 @dbuinfocenter12 @dbuinfocenter12
💔 እናም ጨዋታውን በ 1 ንፁህ ጎል ልዩነት አሸንፈን ነበር በዳኛ ትብብር ዋንጫውን አጥተናል 😭💔💔💔 ተጨዋቾችን ያለቸውን አቅም ሁሉ ስጥተዋል ከነሱ ምንም የቀረ ነገር የለም ኳስ አሸናፊ እና ተሸናፊ አላት ብራቮ psg 👏👏👏👏 አርሰናል በሚቀጥለው ሲዝን የአውሮፓ ዋንጫዎችን ጠራርጎ ይወስዳል 😍 እጅግ አስፈላጊ እና ዋናውን የሊጉን ዋንጫ ማሳካቱ በቂ ነው 👏❤💪 @dbuinfocenter12 @dbuinfocenter12 @dbuinfocenter12