- Последний пост
- 14 авг.
- Последнее чтение
- 08:44
- Постов за неделю
- 31
- Всего постов
- 105
- Тип
- открытый
- Язык
- английский
- Категория
- Образование
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 1 979
- 1/48двое суток
- 2 267
- 1/72трое суток
- 2 446
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
በዲላ ዩኒቨርሲቲ 11 ፕሮግራሞችን በሀገር አቀፍ ደረጃ እውቅና እንዲያገኙ ለማድረግ እየተሰራ ነው። ከየትምህርት ክፍሎቹ የተውጣጡ መምህራን ስልጠና በመውሰድ ላይ ይገኛሉ። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር) በስልጠናው ቦታ በመገኘት ሂደቱን የተመለከቱ ሲሆን፣ መምህራኖቹ ጠንክረው እንዲሰሩ በማበረታታት ዩኒቨርሲቲው አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠውላቸዋል። #የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ!
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
#CALL_FOR_EXTERNAL_REVIEWERS Dilla University cordially invites qualified professionals- university professors and industry experts to participate in an outcome based Educations (OBE) curriculum reviewer validation workshop scheduled for Aug 27, 2026GC. See the poster for more information! #UniversityOfTheGreenland!
"ተወዳዳሪ ዜጋ የሚፈልቅባቸው ሞዴል ትምህርት ቤቶች እንዲሆኑ በትኩረት ይሰራል" ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር) =========*************========= ዲ.ዩ: ነሐሴ 07/2018ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) በዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር)የተመራ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራር ልዑክ ቡድን በዩኒቨርሲቲው ስር የሚገኙ የቅድመ መደበኛ፣ የመጀመሪያ ደረጃ እና የሁለተኛ ደረጃ የኮሚዩኒቲ ትምህርት ቤቶችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል። የየትምህርት ቤቶቹ የስራ ኃላፊዎችም ለልዑካኑ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በየትምህርት ቤቶቹ ያሉ የግብዓት እና ተያያዥ ችግሮችን ለመፍታት የተቋሙ አመራሮች ምልከታ በማድረጋቸው አመስግነው፣ ለተሻለ አፈፃፀም ከአመራሩ ጋር ተቀናጅተው ለመስራት ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ቶሎሳ ዳዲ (ዶ/ር) ባደረጉት ንግግር በየትምህርት ቤቶቹ ያሉ የፋሲሊቲ እጥረቶችን ማሟላት እና ለቀጣዩ የትምህርት ዘመን ዝግጁ የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል። ነገ ላይ ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መጋቢ የሆኑ ትምህርት ቤቶችን መደገፍ ነገን ዛሬ ላይ መስራት በመሆኑ፣ አስፈላጊው ሁሉ ድጋፍና ክትትል ይደረጋልም ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ። መሠረተ ልማት ላይ መስራት ካልተቻለ የሚታሰበውን ብቁ ዜጋ መፍጠር ስለማይቻል፣ ትምህርት ቤቶቹ ያሉበትን ቁመና ማዬታችን ቀጣይ የምንሰራቸውን የቤት ስራዎች እንድንለይ ይረዳናል ብለዋል። ከምልከታው መልስ የኮሚዩኒቲ ትምህርት ቤቶቹ የቅድመ ሁኔታ ግምገማን በተመለከተ የተዋቀረው ኮሚቴ፣ የጥናት ውጤቱን ለፕሬዝዳንቱና ለከፍተኛ አመራሩ አቅርቧል። የሰው ኃይል እጥረት እንዲሁም የአይሲቲ መሠረተ ልማት ጉድለቶች እና ሌሎች እንቅፋቶች ቢኖሩም፣ የመምህራን ትምህርት ከዩኒቨርሲቲው የትኩረት መስኮች አንዱ መሆኑ፣ በቂ የሰው ኃይልና ቤተሙከራዎች መኖራቸው፣ ትምህርት ቤቱን ለመደገፍ ትልቅ አቅም እንደሚሆን በሪፖርቱ ተመላክቷል። ለትምህርት ቤቶቹ የፋይናንስ ድጋፍ ቢደረግ፣ ለመምህራኖቹ ተከታታይ ድጋፍና ክትትል ቢደረግ፣ የመሠረተ ልማት ጥያቄዎች ቢመለሱ አሁን ካለበት የተሻለ ማድረግ እንደሚቻል ተገልጿል። ፕሬዝዳንቱ ትምህርት ቤቶቹ የሚያስፈልጋቸውን የትምህርት ግብዓቶች በቅርበት በመከታተል ተወዳዳሪ ዜጋ የሚፈልቅባቸው ሞዴል ትምህርት ቤቶች እንዲሆኑ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። በትምህርት ቤቶቹ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እና የመሠረተ ልማት ችግሮችን ለመፍታት በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ የገለፁት ፕሬዝዳንቱ፣ በቀጣዩ የትምህርት ዘመን የቅድመ ዝግጅት ስራ ላይ ሁሉም የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎችም ትምህርት ቤቶቹ ደረጃቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ፣ የትምህርት ጥራት እንዲረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ===###=== #የአረንጓዴው_ምድር_ዩኒቨርሲቲ #UniversityOfTheGreenland
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи