Ministry of Education Ethiopia
СтатистикаThis is Ministry of Education's Official Telegram Channel. For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe
- Последний пост
- 14 авг.
- Последнее чтение
- 12:18
- Постов за неделю
- 16
- Всего постов
- 22
- Тип
- открытый
- Язык
- английский
- Категория
- Новости и СМИ (по похожим)
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 12 101
- 1/48двое суток
- 15 599
- 1/72трое суток
- 16 824
Медиана по постам, которые мы застали свежими и померили через сутки.
Посты
видео или голосовое, без подписи
+1
ማስታወቂያ የትምህርት ሚኒስቴር ለልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች (Special Boarding Schools) ርዕሰ መምህራን ለመቅጠር ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም. በበይነ መረብ (Online) ባወጣው የቅጥር ማስታወቂያ መሠረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተጠቀሰ አመልካቾች ለፈተና የተመረጣችሁ ስለሆነ ማክሰኞ ነሐሴ 12 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 8:00 በትምህርት ሚኒስቴር ዋና መሥሪያ ቤት አዳራሽ ተገኝታችሁ የጽሑፍ ፈተና እንድትወስዱ እናሳውቃለን። ማሳሰቢያ፦ ተወዳዳሪዎች ለፈተና ስትመጡ የሥራ ልምድ መረጃ፣ ዋናውን የትምህርት ማስረጃ (Original) እንዲሁም በቅጥር ማስታወቂያው ላይ የተጠቀሱትን ሌሎች አስፈላጊ ዶክመንቶች ዋናውንና ኮፒውን (Original & Copy) በተጨማሪም ማንነታችሁን የሚገልፅ መታወቂያ ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን።
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
+4
በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚሰሩ መምህራንና የትምህርት ባለሙያዎችን ሙያዊ አቅም ለማሰደግ የሚረዳ የኣይሲቲ ቴክኖሎጂን ወደ ተግባር ለማስገባት እየተሠራ መሆኑ ተገለፀ፤ ---------------------------- // ----------------------------- (ነሐሴ 06/2018 ዓ.ም) ትምህርት ሚኒስቴር ከዩኔስኮና የጃፓን መንግሥት ጋር በመተባበር የትምህርት ባለሙያዎችን ሙያዊ አቅም ለማሰደግ የሚረዳ ተንቀሳቃሽ የኣይሲቲ ቴክኖሎጂ ቁሳቁሶችን ለሚመለከታቸው ተቋማት አስረክቧል። በዚሁ ወቅት በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት ተ/መሪ ሥራ አስፈፃሚ የሆኑት ወ/ሮ አሰግድ ምሬሳ ባስተላለፉት መልዕክት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚሰሩ መምህራንና የትምህርት ባለሙያዎችን ሙያዊ አቅም ለማሰደግ የሚረዳ የኣይ ሲቲ ቴክኖሎጂ ፕሮጀክትን ወደ ተግባር ለማስገባት እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል። የፕሮጀክቱ ተጠቃሚዎች 35 የሚደርሱ የመምህራን ትምህርት ኮሌጆች እና በመምህራን ትምህርት ላይ ትኩረት አድርገው እየሰሩ ያሉ 5 የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል። ፕሮጀክቱ የኢትዮጵያ መንግሥት በሁሉም ዘርፍ ሀገሪቷን ለማዘመን እና የትምህርትና ሥልጠና ሥርዓትን ለማጠናከር በቁርጠኝነት እየሠራቸው ላሉ ሥራዎች አዎንታዊ ድጋፍ የሚሰጥ መሆኑንም አንስተዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://web.facebook.com/share/p/1BSzqkrubF/
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
+2
የመምህራን ስልጠና እና የተግባር ተኮር ትምህርት ማስተማሪያ ሞጁል ዝግጅት ጥራትን እና ወጥነትን ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው። --------------------------------- // ------------------------------- (ነሐሴ 05/2018 ዓ.ም) የትምህርት ሚኒስቴር ከፊንላንድ መንግስት ጋር በመተባበር ባዘጋጀው የመምህራን ትምህርት ስልጠና እና የተግባር ተኮር ትምህርት ማስተማሪያ ሞጁል ዝግጅት ማዕቀፍ ላይ ዓውደ ጥናት ተካሂዷል። የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍን በመወከል በመድረኩ የተገኙት የጎልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርት መሪ ስራ አስፈጻሚ ዬሴፍ አበራ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክት የትምህርት ጥራትና ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ በሚከናወኑ ስራዎች አካታችነትና ፍትሃዊነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የሚዘጋጁት የመምህራን ትምህርት ማሠልጠኛ ሞጁሎች የመምህራንን ሙያዊ አቅም በከፍተኛ ደረጃ የመገንባት እና በሥርዓተ ትምህርቱ ውስጥ የሚታዩ የጥራት ክፍተቶችን በዘላቂነት ለመፍታት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ መሆኑንም ገልጸዋል። ማሪያ ማቲር የ”Teacher Education for Inclusion and Quality (TEFIQ)” ፕሮጀክት በኢትዬጵያ አስተባባሪ በበኩላቸው የመምህራን ትምህርት ማሰልጠኛ ተቋማት ውስጥ ያለውን የሞጁልና ሌሎች መሰል የትምህርት ፓሊሲ ማስፈፀሚያ ዶክመንቶች ዝግጅት ወጥነትና ጥራትን በማረጋገጥ ሂደት ውስጥ የዘርፉ ባለሙያዎች ሚናቸውን በአግባቡ መወጣት እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://web.facebook.com/share/p/17QVX6g282/
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
+3
የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በታንዛኒያ የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች ብድር ቦርድ ዋና ዳይሬክተር የተመራ የልዑካን ቡድን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግሩ። -------------------------- // ----------------------- (ነሐሴ 05/2018 ዓ.ም) በሁለቱን ሀገራት መካከል በዘርፉ የልምድ ልውውጥና የጋራ ትብብርን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተደርጓል። የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በታንዛኒያ የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች ብድር ቦርድ ዋና ዳይሬክተር በዶ/ር ቢል ኪዊአ የተመራ የልዑካን ቡድንን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ብቃትና አቅም በማሳደግ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን ገልጸውላቸዋል። በኢትዮጵያ በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሚማሩ ተማሪዎች የሚያገኙትን የትምህርትና የአገልግሎት ወጪ የሚካፈሉበት የወጪ መጋራት (Cost Sharing) ሥርዓት ተዘርግቶ ተግባራዊ እየተደረገ እንደሚገኝም ተናግረዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://web.facebook.com/share/p/1D4w2mcc5k/
ማስታወቂያ ለፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች የ9ኛና የ10ኛ ክፍል ተማሪዎችን ለማስተማር ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል። በዚህም ለ10 ክፍል ተመዝጋቢዎች የተጠቀሰው 95% ወደ 85 % ዝቅ ያለ መሆኑን አውቃችሁ 85% እና በላይ ያላችሁ የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። ለመመዝገን ይህንን ሊንክ ጥጫኑ፤ https://sbs.moe.gov.et/apply
ማስታወቂያ ትምህርት ሚኒስቴር በፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች የ9ኛና የ10ኛ ክፍል ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል። በመሆኑም መስፈርቱን የምታሟሉ ተማሪዎች በዚህ ሊንክ https://sbs.moe.gov.et/apply መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи