ከህይወት ገፅ የግጥም መድብል
Статистика........ኑ ስሜትን በግጥም እንግለፅ ትውልድን በጥበብ እናንፅ ። የፍቅር ቤት እዚህ ነው ! አሰተያየት ካላችሁ 👇 @fikee12 ላይ ማድረስ ይቻላል
- Последний пост
- 13 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 1
- Всего постов
- 21
- Тип
- открытый
- Язык
- ti
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 156
- 1/48двое суток
- 178
- 1/72трое суток
- 192
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
ሁሉም ሲጠምም ቀን ሲከፋብን ኃጢያቱ በዝቶ ፀሎት ጠፋብን ። ፍቃዱ ግርማ / ዘ-በኩር / t.me/fikee21
ሁሉም ያልፋል ። አልኩኝ ለብቻዬ
без подписи
без подписи
እኔኑ ገረመኝ የጥርሴ ክፋቱ ማታ ሊያስለቅሰኝ ከሰው ፊት መፍካቱ ። ፍቃዱ ግርማ / ዘ -በኩር / t.me/fikee21
መኖር ምን ሆኖ ነው እንዲህ የሚያደክመው...... ? Elias shitahun t.me/@fikee21
ሰው ግን ምን አይነት ክፉ ፍጥረት ነው በማርያም ።
ሰው ግን እራሱን እንዴት ነው የሚያየው? ተንቀሳቃሽ አፍር መሆኑን ይረሳል ይገርመኛል ። ፍቃዱ ግርማ / ዘ-በኩር/ t.me/fikee21
ሻማዬን ለኩሼ እጣኑን አጭሼ በቀጤማ ጉዝጎዝ ቤቴን አሳምሬ ከአንድ ጠርሙስ ጋር ብርጭቆ ደርድሬ ሽር ጉድ እያልኩኝ ስጠብቅሽ ውዬ መቅረትሽ ሳይገባኝ ፣ ከንቱ ነው የደከምኩ ትመጫለሽ ብዬ ። ፍቃዱ ግርማ / ዘ-በኩር / t.me/fikee21
без подписи
ይቅር በለን ( በእውቀቱ ስዩም) የዘራም አጨደ ያጨደም አስገባ ያስገባም ጋገረ የጋገረም በላ" ከዚያ ምን ይመጣል ፍርፍር ሆኖ ገብቶ: ፍግ ሁኖ ይወጣል:: በሸመታም ይሁን: በወራሪ ዝርፍያ በስርአት ይሁን : በሽምያ በግፍያ በግብዣም ይድረሰን: ወይ በመቀላወጥ የምንበላው ህብስት: የምንጨልፈው ወጥ ማለፍያው ሰርገኛው: ዶሮና ምስሩ ወደታች ስንምሰው : ብዝበዛ ነው ስሩ:: የርግማኑን ራስ : ሆድ ይዘን ተፈጥረን መቸገር ሳያንሰን ለጠበቃ አልባዎች ሸክም አሸጋግረን ከጥንት እስከዛሬ ጭንቅህን በልሳን ተርጉመህ ባትነግረን ይቅር በለን በሬ አህያ ሆይ ማረን!!
ብዙ ግዜ አያቴ ጋር ቁጭ ብዬ የምትነግረኝ እሰማት ነበር ። አንድ ቀን ማታ ቁጭ ብለን ሰለነጌ መጨነቀን እያወራን ነብር ። ከማሃል አያቴ ስሙ ልጆች ስትል ቀጠለች ። ንጉሱ የሆነችን ሴት ነጌ ጣዋት ሁለት አንገት ያለው ፈረስ ካላመጣሽ ከነ ቤተሰብሽ እስራት ነው የማስተላለፍባችሁ ይላታል ። ሴትዮዋ ጨነቃት ጠበባት እናም ወደ ጎረቢት ሄዳ ትቀመጣለች ትነሳለች ግራ የተጋቡት ጎረቢቶቿ ምን ሆነሻል ሲሉ ጠየቋት ? ንጉሱ ያላትን ነገር ነገረቻቸው አንዱ ሰውዬ እና ለዚ ነው የምትጨነቂው አላት? አዎ አለች ። ሰውዬው አይዞሽ ለሊቱን ወይ ሁለት አንገት ያለው ፈረስ ተወልዶ ያድራል ወይ ንጉሱ ይሞታሉ ዝም ብለሽ ተኚ አላት ። ሲነጋ ንጉሱ ሞቱ ተበለ ። አያችሁ ነጌን አቅዱ እንጂ አትጨነቁ አለቺን አያቴ ። t.me/fikee21
Channel photo updated
እድሜ ለበደልሽ እድሜ ለጭካኔሽ እድሜ ላንቺ ክፋት ላንቺ ይብላኝ እንጂ... እኔማ..... እንደ ምንም ብዬ ያቺን ቀን አለፍኳት ። እድሜ ላንቺ እድሜ ኑሪ ነፍ አመት ማድመጥ ጀምሪያለሁ የእራሴን ልብ ምት ምንድን ነው ትዝታ ምን ያደርጋል ናፍቆት ምን ያደርጋል ትላንት ምን ያደርጋል ፀፀት ላለፈ እንደ ዘበት ። እና ወደ አሻሽ ሂጂ ያሻሽን አፍቅሪ ያሻሽን ውደጂ ከኔ የተሻለ ሰው አግኝተሽ እንደሁ ይቅናሽ ብዬሻለሁ ። ፍቃዱ ግርማ / ዘ-በኩር / t.me/fikee21
በሀሳብ ተውጬ እጄን በአፌ ጫንኩኝ ማታ ባልሺኝ ነገር ፈገግ ስል ዋልኩኝ ይጎሰማል እሄው ልቤ እንደ ከበሮ ይወዘወዘኛል ያንቺው ፍቅር አስሮ ። ፍቃዱ ግርማ / ዘ-በኩር / t.me/fikee21
❝ዝም ስትል የማታውቅ የሚመስላቸው ብዙ ናቸው..ምክንያቱም እነሱ በማውራት ያምናሉና ነገር ግን ያወሩትን አይኖሩትም።...አንተ ግን በማውራት አትመን ዝም ብለህ ልታወራ የፈለከውን ኑረው ከዛም ባንተ ዝምታ ውስጥ የኖርከው ህይወት ጥሶ ይወጣና አንተ ዝም እንዳልክ ሳታወራ ሰዎች ያወሩልሃል።❞ "እመጓ" ( ዶ/ር አለማየሁ ዋሴ እሼቴ / t.me/fikee21
በእውቀቱ_ስዩም አገሬ አገርን ለፈሪ፥ አይሰጡም አደራ ዳር አድርጎት ያድራል፥ የማሀሉን ስፍራ፤ አገርን ለፈሪ፥ አደራ ብሰጠው የዘላለም ቤቴን፥ ባንድ አዳር ለወጠው፤ አባ ነጋ ሞቶ አባ ጽልመት መጥቶ አገሬ እንደ ዛጎል፥ እያብረቀረቀች ከባሕር ተገፍታ፥ የብስ ላይ ወደቀች።
የፍየል ወጠጤ ፣ ትክሻው ያበጠ ልቡ ያበጠበት እንዋጋ ብሎ ከነብር ላከበት ። አሉ ። t.me/fikee21
መድፉ ሳይተኮስ ቦምቡ ሳይፈነዳ ያ ሁሉ መኩዋንንት እንደ በግ ተነዳ ። t.me/fikee21
ትጎዛለች አህየው በውጥንቅጥ መኖር ሀሳብ ተሸክማ ተራራ የሚያክል እናት ግን መቼ ነው ልቧ እርፍ የሚል ? መቼ ነው የሷ ቀን ለራሷ የምትኖረው ልጄ ሳትል ወላ ሌቱን የምታድረው መቼ ነው ? እናትነት የማይፈታ ሚስጥር ። ፍቃዱ ግርማ ( ዘ - በኩር )