Harun Media - ሀሩን ሚዲያ
Статистика- Последний пост
- 15 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 21
- Всего постов
- 41
- Тип
- открытый
- Язык
- und
- Категория
- Новости и СМИ (по похожим)
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 2 469
- 1/48двое суток
- 2 829
- 1/72трое суток
- 3 051
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
видео или голосовое, без подписи
https://youtu.be/SYldFtDRdco?si=ngMdchD_gdHP7-cV
የደብረ ታቦር መስጂድ ግንባታን ለመደገፍ ታላቅ የኦንላይን የገቢ ማሰባሰቢያ ሊካሄድ ነው! • ሀሩን ሚዲያ | ነሐሴ 8 ቀን 2018 ዓ.ል በደቡብ ጎንደር ዞን የምትገኘው ደብረ ታቦር ከተማ ከ700 ዓመታት በላይ ዕድሜ ያስቆጠረች ቢሆንም፤ በዚህች ታሪካዊ ከተማ የሚገኘው አንድ መስጂድ ብቻ ነው። ይህ ነባር መስጂድ ከከተማዋ የሙስሊም ማኅበረሰብ ቁጥር አንጻር በቂ ባለመሆኑ፣ የአካባቢው ሙስሊም ማኅበረሰብ ያለውን አቅም በማስተባበር አዲስ የመስጂድ ግንባታ መጀመሩ ተገልጿል። የግንባታው ዋነኛ ዓላማ ከመስጂድ ግንባታ ባሻገር፤ ለአካባቢው ሙስሊም ማኅበረሰብ ሰፊና ዘርፈ ብዙ ጥቅም የሚሰጥ ተቋም መገንባት መሆኑ ተጠቁሟል። ይሁን እንጂ የግንባታውን ወጪ በከተማዋ ሙስሊሞች አቅም ብቻ ማጠናቀቅ የማይቻል በመሆኑ፣ በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ሙስሊሞች አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል። በመሆኑም በመጪው እሁድ ነሐሴ 10 ቀን 2018 ዓ.ል ታላላቅ ዑለማዎች፣ ኡስታዞችና ታዋቂ ግለሰቦች የሚሳተፉበት ታላቅ የኦንላይን የገቢ ማሰባሰቢያ መድረክ እንደሚካሄድ ታውቋል። ይህ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ከነሐሴ 10 እስከ ነሐሴ 12 ቀን 2018 ዓ.ል የሚቆይ ሲሆን፤ መላው ሙስሊም ማኅበረሰብ በመሳተፍ ለመስጂዱ ግንባታ የበኩሉን አሻራ በማሳረፍ የአጅሩ (የምንዳው) ተቋዳሽ እንዲሆን አዘጋጅ ኮሚቴው ጥሪ አቅርቧል። 📅 ረቢዑል አወል 1 ቀን 1448 ዓ.ሂ © ሀሩን ሚዲያ
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
የዲያስፖራ ልዑካን በአወሊያ ተቋም እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎችን በማድነቅ አጋርነታቸውን አረጋገጡ! • ሀሩን ሚዲያ | ነሐሴ 7 ቀን 2018 ዓ.ል በ1950ዎቹ በአንድ የየመን ኡስታዝ ጅማሮውን ያደረገው ዕድሜ ጠገቡ አወሊያ የልማትና እርዳታ ድርጅት፤ በቅጥር ግቢው ውስጥ የሚገኙትን ሆስፒታል፣ ትምህርት ቤት፣ የጀናዛ ማጠቢያ ክፍል፣ የእግር ኳስ ሜዳና መስጂድ ለልዑካኑ አስጎብኝቷል። በጉብኝቱ ላይ ከተሳተፉት የዲያስፖራ ተወካዮች መካከል፦ • ኡስታዝ ሙክታር ጀማል (በእንግሊዝ የነጃሺ መስጂድ ኢማም) • ማህሙድ ሳዲቅ (በካናዳ ቶሮንቶ የኖርዝ ኢስላሚክ ሴንተር ሊቀመንበር) • አሳድ ሙሐመድ (በስዊድን የኢትዮጵያ ሶማሌ ተወካይ) • ሙሐመድ ደጉ (የፈርስት ሂጅራ መስጂድ ኢማም) • ነዋዊ ሙሳ (የደቡብ አፍሪካ ኢትዮጵያውያን ማህበር ሊቀመንበርና ተወካይ) • አብዱራዛቅ ሙሐመድ (የኦሮሞ ማህበር ሊቀመንበር) እና • ኢንጅነር አሊ ላሳን (በስዊድን የአፋር ማህበር ተወካይ) ይገኙበታል። የጉብኝቱን መርሃ ግብር የአወሊያ የልማት ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ጀማል ሙሐመድ፣ የድርጅቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ኡስታዝ ጀማል ፈንታውና ሌሎች የድርጅቱ ኃላፊዎች መርተውታል። የዲያስፖራ ተወካዮቹ በተቋሙ የተከናወኑትን ሥራዎች ያደነቁ ሲሆን፤ “ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ስንጎበኝ የተሰማንን ደስታ፣ በአወሊያ የልማትና እርዳታ ድርጅት ሥራዎች ላይ በድጋሚ አረጋግጠናል” በማለት የተቋሙን ዳግም ማንሰራራት አድንቀዋል። አክለውም አወሊያ ዕድሜ ጠገብ ተቋም እንደመሆኑ፣ ታሪኩን የሚመጥን ሥራ ለማከናወን በአመራሩ እየተደረገ ያለውን ጥረት እንደሚደግፉና ከድርጅቱ ጎን እንደሚቆሙ ቃል ገብተዋል። ድርጅቱ በቅርቡ 75ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እንደሚያከብር ተገልጿል። © ሀሩን ሚዲያ
https://youtu.be/cg1axGQFKp4?si=wLEggSU2nlkUvPvg
https://youtu.be/iYLkYlPuZRA?si=NiIgmqz43BeQSVx-
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
ዳሽን ባንክ 'ሸሪክ' ከወለድ ነጻ አገልግሎት 50 የቢዋይዲ (BYD) ኤሌክትሪክ መኪኖችን ለኤሌጋንስ አስመጪና ላኪ አስረከበ! • ሀሩን ሚዲያ | ነሐሴ 5 ቀን 2018 ዓ.ል ዳሽን ባንክ በ'ሸሪክ' ከወለድ ነጻ የፋይናንስ ሥርዓት በኩል ያቀረባቸውን 50 ዘመናዊ የቢዋይዲ (BYD) ኤሌክትሪክ መኪኖችን ለኤሌጋንስ አስመጪና ላኪ በይፋ አስረክቧል። መኪኖቹ በሜትር ታክሲ አገልግሎት ላይ የሚውሉ ሲሆን፣ በርካታ ወጣቶችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንደሚያደርጉ ተገልጿል። በሸራተን አዲስ ሆቴል በተካሄደው የርክክብ ሥነ-ሥርዓት ላይ የተገኙት የዳሽን ባንክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት ዋና ኦፊሰር አቶ አምዱ ሰማን በንግግራቸው፤ ዳሽን ሸሪክ ባለፉት ስምንት ዓመታት ከ1.6 ሚሊዮን በላይ ደንበኞችን ማፍራቱን አስታውቀዋል። አክለውም የደንበኞች ተቀማጭ ገንዘብ 30 ቢሊዮን ብር መድረሱንና ከዚህ ውስጥ 18 ቢሊዮን ብሩ ለተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች በከወለድ ነጻ የፋይናንስ ሥርዓት መቅረቡን ጠቁመዋል። ይህም ለሀገር ውስጥ ምርታማነትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን አብራርተዋል። 50ዎቹን መኪኖች የተረከቡት የኤሌጋንስ አስመጪና ላኪ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ቶፊቅ ሙሐመድ፤ ዳሽን ሸሪክ ለድርጅታቸው ላሳየው እምነትና ለሰጠው የፋይናንስ ድጋፍ ምስጋና አቅርበው፣ ድርጅታቸው ከባንኩ ጋር ያለውን ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። በርክክብ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ እንደተገለጸው፤ ይህ የፋይናንስ ድጋፍ በ50ዎቹ መኪኖች ብቻ የሚያበቃ ሳይሆን በቀጣይም ለሌሎች ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠርና ሥራ ፈጣሪዎችን ለመደገፍ የከወለድ ነጻ የፋይናንስ አገልግሎቱ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተመላክቷል። 📅 ሰፈር 28 ቀን 1448 ዓ.ሂ © ሀሩን ሚዲያ