አዲስ ሪፖርተር - NEWS
Статистика🔖 ይህ የአዲስ ሪፖርተር የቴሌግራም ገፅ ነው ! => በቻናሉ 📌 ፈጣን ፥ 📌 ትኩስ ፥ 📌 ወቅታዊ እና 📌 አዳዲስ መረጃዎች እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል ! 🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል ! For promotion @Addisreporter_bot #ADDIS ABABA, ETHIOPIA
- Последний пост
- 15 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 69
- Всего постов
- 131
- Тип
- открытый
- Язык
- ti
- Категория
- Новости и СМИ
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 4 239
- 1/48двое суток
- 4 857
- 1/72трое суток
- 5 238
Медиана по постам, которые мы застали свежими и померили через сутки.
Посты
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
የሕግ ባለሙያዎች ባቀረቡት አቤቱታ መሠረት የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በጠበቆች ላይ ተጥሎ የነበረውን የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ምዝገባ አገደ። የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የገቢዎች ቢሮ፣ የሕግ ባለሙያዎች (ጠበቆች) ከተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ምዝገባ ጋር በተያያዘ ላቀረቡት አቤቱታ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የዕግድ ትዕዛዝ ማስተላለፉን አሳውቋል። ቢሮው ለዞንና ለከተማ አስተዳደር የገቢ መሥሪያ ቤቶች ባስተላለፈው ማብራሪያ ፣ በጥብቅና ስራ የተሰማሩ የሕግ ባለሙያዎች በገንዘብ ሚኒስቴር በወጣው መመሪያ ቁጥር 1104/2018 መሠረት ለተጨማሪ እሴት ታክስ እንዲመዘገቡ ተሰጥቶ የነበረው ድንጋጌ ላይ የመመሪያ ክለሳ አቤቱታ ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት አቅርበው ነበር። የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የቀረበውን አቤቱታ ተመልክቶ በጉዳዩ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ፣ ጠበቆች ለተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) እንዲመዘገቡ የሚያዘውን መመሪያ በጠበቆች ላይ ተፈጻሚ እንዳይሆንና በዕግድ እንዲቆይ ትዕዛዝ ሰጥቷል። በመሆኑም በፍርድ ቤቱ የተለያዩ መዝገቦች የታገዱ ጉዳዮች መኖራቸውን ቢሮው አረጋግጧል። ነገር ግን የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ምዝገባው በዕግድ መቆየቱ፣ ጠበቆችን ከሌሎች የግብር ግዴታዎች ነፃ እንደማያደርጋቸው ያሳሰበው ቢሮው ማንኛውም የሕግ ባለሙያ (ጠበቃ) የንግድ ሥራ ገቢ ግብሩን በተመለከተ በክልሉ የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 301/2018 መሠረት የመክፈል ግዴታው እንደጸና ነው ብሏል። ባለሙያዎቹ እንደ ደረጃ "ለ" ግብር ከፋይነታቸው የሒሳብ መዝገብ የመያዝ ወይም በታወቀው የገቢ ማሳወቂያ ቅጽ (Form) መሠረት ግብራቸውን በወቅቱ የማሳወቅ ግዴታ አለባቸው ነው ያለው። ይህ የፍርድ ቤት ዕግድ የሚያገለግለው ከተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ጋር ለተያያዘው ጉዳይ ብቻ መሆኑን የገለጸው ቢሮው፣ የንግድ ሥራ ገቢ ግብራቸውን በሒሳብ መዝገብ የማያሳውቁ ጠበቆች እንደግብር ከፋይነታቸው ከነሐሴ 1/2018 ዓ.ም ወይም ከህዳር 1/2019 ዓም ጀምሮ በሦስተኛ ወገን ወይም በግምት የንግድ ስራ ገቢ ተወስኖ እንዲያሳውቁ እንዲደረግ ማሳሰቢያ ሰጥቷል። የሂሳብ መዝገብ መያዝ የሚገባቸው ግብር ከፋዮችም ግዴታቸውን ካልተወጡ በአዋጁ የተደነገጉ አስተዳደራዊ ቅጣቶችም ተፈጻሚ እንደሚሆኑባቸው አሳውቋል። በሌላ በኩል የፌደራል ጠበቆች ማህበር የጠበቆችን የግብር አከፋፈል ሁኔታ በተመለከተ እያከናወናቸው ስላላቸው ስራዎች ለአባላቱ በሰጠው ማብራሪያ በጉዳዩ ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተከታታይ ውይይቶችን እያደረገ ስለመሆኑ አንስቷል። ማህበሩ ጠበቆች ከ«ለ» ደረጃ ግብር ከፋይነት ውጪ ተደርገው የሂሳብ መዝገብ እንዲይዙ የሚጠየቁበትን አዲሱን አሰራር በመርህ ደረጃ ተገቢ እንዳልሆነ ያምናል ያለ ሲሆን ይህም በሕግ ማሻሻያ ሊታረም የሚገባ ጉዳይ መሆኑን ከመንግስት አካላት ጋር በቀጣይነት እያነሳ ይገኛል ብሏል። በዚህ ምክንያት መመሪያው እስኪወጣ ድረስ ጠበቆች እንደ ቀድሞው አሰራር በተመጣጣኝ የገቢ መቶኛ ተቀናሽ ስሌት መሠረት ግብራቸውን እንዲከፍሉ ጊዜያዊ አሰራር እንዲፈቀድ ማህበሩ መጠቁን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ማህበሩ ከሰጠው ማብራሪያ ላይ ተመልክቷል። Via : ቲክቫህ @Addis_Reporter @Addis_Reporter
без подписи
без подписи
በርካሽ ድሮን ሚሊዮን ዶላር ማሳጣት‼️ ኢራን የአሜሪካን የአየር መከላከያ አቅም ለማዳከም ርካሽ ድሮኖችን እየተጠቀመች መሆኑ ተገለጸ❗❗ ኢራን ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ርካሽ የ«ሻሄድ» (Shahed) አይነት አጥቂ ድሮኖች ከባለስቲክ ሚሳይሎች ጋር በማቀናጀት የአሜሪካን እና አጋሮቿን የአየር መከላከያ ስርአት በመፈታተን ላይ እንደሆነ ተዘገበ። የኢራን ስትራቴጂ ዋና ዓላማ በእያንዳንዱ ድሮን ኢላማን መምታት ሳይሆን፣ በተደጋጋሚ በሚላኩ የድሮን ማዕበሎች የአሜሪካን የመከላከያ አቅም ማድከም ነው። ይህ አካሄድ የአሜሪካን ውድ ሚሳይሎች (ኢንተርሴፕተሮች) በዝቅተኛ ዋጋ በሚገመቱ የኢራን ድሮኖች ላይ እንዲባክኑ በማድረግ፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል የኢኮኖሚ እና የመከላከያ አቅም ሚዛን መዛባትን እንዲፈጠር እያደረገ መሆኑን ወታደራዊ ተንታኞች ይገልጻሉ። @Addis_Reporter @Addis_Reporter
ባንዳ ለሆዱ ሲሞት እኛ ለሀገር ሉዓላዊነት ለህዝቦች ክብርና አንድነት እንሞታለን-ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ‼️ ሻዕቢያ ከጅምሩ ኢትዮጵያን ከባህር በር ለማራቅ ከታሪካዊ ጠላቶቻችን ጋር ፅምዶ ፈጥሮ ኢትዮጵያ ላይ ደባ የሰራ ሃይል ነው ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ህወሃትም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ የሸጠና ለ27 አመታት ስልጣን ይዞ ኢትዮጵያ የባህር በር እንድታጣ አጠንክሮ የሰራ ቅጥረኛ የገዛ አገሩን ሠራዊት ያጠቃ የክህደት ሃይል ነው ብለዋል ። ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ በሕወሃት ክህደት የተፈተነች ነገር ግን ፀንታ የቆመች የልዩ ዘመቻ ሠራዊት መሰል ጠንካራ አርበኛ ልጆች ያሏት አገር ስለሆነች ጉዞዋን ቀጥላለች ብለዋል። የጥፋት ሃይሎች በባዕዳን ስትራቴጂ ሥር ተሰልፈው ኢትዮጵያን የማዳከምና የማፍረስ ፅምዶ የተባለ ጥምረት ቀርፀው ሕዝባችንን ለስቃይና መከራ በመዳረግ ደካማ ኢትዮጵያን ለማየት ጓጉተው ቢሠሩም ይህ ፍላጎታቸው መቼም ሊሳካ እንደማይችል አሳይተናቸዋል ብለዋል። ወያኔ የኢትዮጵያን ህዝብ በመከፋፈል እርስ በእርሱ እንዳይተማመን ያደርግ እንደነበረ አውስተው የትግራይን ህዝብ ደግሞ የኢትዮጵያ ልጆች እየመጡብህና እየከበቡህ ነው እያለ ከወንድም የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በጠላትነት እንዲተያይ ሲሰራ የኖረ እኩይ ፖለቲካ አራማጅ ፀረ አገር ሃይል ነው ብለዋል። @Addis_Reporter @Addis_Reporter