tgindex
نَـحْـنُ أَبْـنَاءُ السَّلفِــيِّينْے

نَـحْـنُ أَبْـنَاءُ السَّلفِــيِّينْے

Статистика

فليس العلم بكثرة الرواية ولا بكثرة المقال. ولكنه نور يقذف فى القلب يفهم به العبد الحق ويميز به بينه وبين الباطل. /هـ አስታያየቶዎንና ምክሮዎን⇩ @Nehnu_abnau_aselefiyin_bot በዚህ ያድርሱን👆

Последний пост
14 авг.
Последнее чтение
15 авг.
Постов за неделю
7
Всего постов
22
Тип
открытый
Язык
арабский
Категория
Новости и СМИ (по похожим)
В каталоге с
13 авг.
Подписчики
5 966
+9 за 2 дн.
Сутки
0
0,00%
Неделя
 
Месяц
 
Просмотров на пост
2 201
22 постов
Вовлечённость
36,9%
к подписчикам
Постов в день
1,0
всего 22
Упоминаний
14
каналов
Охват размещения
оценка
1/24сутки в ленте
1 264
1/48двое суток
1 448
1/72трое суток
1 562

Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.

Посты

  • ነጠላ ሰረዝ ታውቃለህ አይደል? ፅሁፍ ላይ አስፈላጊ ነው። ቃላትን ትለይበታለህ፣ ዝርዝር ሃሳብህን ትጠቅስበታለህ። ነገር ግን በድምፅ አታነበውም፣ ትፅፈዋለህጂ። እናልህ፤ ህይወትህ ላይ አንዳንድ ሰዎች አሉ፤ ክፉ ደጉን ትለይባቸዋለህ። ትምህርትህ ናቸው። ግን “ምን አሉ?” ብለህ አትጮህም። “በምን አሙኝ?” ብለህ ዋይታህን አታሰማም። ይፃፋሉ፤ ግን አይነበቡም !! t.me/abdu_rheman_aman t.me/abdu_rheman_aman

  • ሰዎች ሆይ ! 📀 ሸይኽ ሙሐመድ መህሩስ t.me/abdu_rheman_aman t.me/abdu_rheman_aman

  • ​በህይወትህ መንገድ ላይ ያለ ምንም ዝግጅት የምታቅፋቸው ስጦታዎች እንዳሉ ሁሉ፣ ጥርስህን ነክሰህ የምታልፋቸው የፈተና ዳገቶች ያጋጥሙኃል። አንዳንዴ ተስፋህ ጨልሞ ሂወትህ በእንባ የራሰ ይመስልኃል፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ የደስታህ ብርኃን የጨለማውን በር ጥሶ ሲበራ ታየዋለህ… ​የሚሳኩ ህልሞችህ ይገርሙህና፣ ሳትይዛቸው የሚበኑ ተስፋዎችህ ያስደነግጡኃል። ግን ሁሌም ቢሆን በገዛ እጅህ ልትጽፈው የደከምክለት ሳይሆን፣ በአላህ ብዕር የተፃፈው ታሪክህ ይበልጥ ያምራል። ሁሌም ቢሆን የአላህን ውሳኔ ወደህ ተቀበል !! t.me/abdu_rheman_aman t.me/abdu_rheman_aman

  • 11 авг.1 52916

    ከፊሉ ልጅ የለኝም ብሎ ያለቅሳል። ሌላውን ልጁ ያስለቅሰዋል። ከፊሉ እህት ወንድም የለኝም ብሎ ይከፋዋል። ሌላው በእህት በወንድሞቹ ውስጡ ቆስሏል። ዱንያ አጃዒቧ አያልቅም። ግማሹ በመከራ፣ ሌላው በጥጋብ ያለቅሳል። "እናቱ የሞተችበትና፣ ገበያ የሄደችበት እኩል ያለቅሳል" በሚለው አገርኛ ብሂል ውስጥ ህመም አለ። መከራ ሁሉ አንድ አይደለም። ከባሰም በላይ ብዙ የባሰ እንዳለ በማስተዋል "አልሐምዱ ሊላህ" እንበል። = የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/IbnuMunewor https://t.me/IbnuMunewor

  • 10 авг.1 56414

    በሲህር ምክንያት ሰዎች ቀብር ገብተዋል፤ ጤናቸውን ተነፍገዋል፤ ሰላማቸውን አጥተዋል፤ ፍቅር እና ደስታ እርቋቸዋል፤ የገንዘብ ህይወታቸው ተዘበራርቋል፤ ትዳራቸው ተበትኗል... ​ ይህ ሁሉ እየሆነ ሳለ፣ አንድ ተጎጂ በሰው ዐይን ወይም በሲህር ምክንያት ችግር ገጠመኝ ሲል፣ "ቆንጆ ነኝ፣ ሀብታም ነኝ፣ ታዋቂ ነኝ" እያለ እንደሆነ አድርገን የምንተረጉመው ለምንድነው ?፤ ​አንዳንዶች ደግሞ የሰውየውን የእምነት እና የአስተሳሰብ ጥንካሬ ጥያቄ ውስጥ የሚከቱም አሉ። ነገር ግን ነብያችን ﷺ "የሰው ዐይን ሀቅ ነው" በማለት አስተምረውናል፤ የህይወት ተሞክሯችንም የሚያረጋግጠው ይህንኑ ነው። ካላወቅን መጠየቅ ደግ ነው፤ ችግሩን በሚያውቅ እና ገፈቱን እየቀመሰ ባለ አካል ላይ ለመሳለቅ መሞከር ግን አላዋቂነት ነው። ​በቁም በፈላ ዘይት ውስጥ እንዲነከሩ ከምመኛቸው ሰዎች መካከል ሳሂሮች እና አስደጋሚዎች ግንባር ቀደሞቹ ናቸው። አላህ ያዋርዳቸው !! t.me/abdu_rheman_aman t.me/abdu_rheman_aman

  • 9 авг.1 84111

    አንዳንድ ወንድሞች ለአጅነብይ ሴት ያላቹህን መልካምነት እና ትህትና .. ለኒካህ ሚስታቹህ ብታደርጉት አንድም ትዳር ባልፈረሰ ነበር !! t.me/abdu_rheman_aman t.me/abdu_rheman_aman

  • 9 авг.1 4267

    ጌታዬ! አንተን እንዳውቅ በማድረግ ለዋልክልኝ ውለታ በቂ የምስጋና ቃላት የለኝም። በፈጠርካቸው ፍጡራን እና መሬት ላይ በዘራኸው አፈር ልክ ምስጋና ይገባህ። ምስጋና የተባለ፣ መጀመርያውም መጨረሻውም ሁሉ ለአንተ ይሁን! ​ረቢ! ከዚህ በላይ ልወቅህ፤ ከዚህ በላይ ልውደድህ፤ ከዚህ በላይ ልጠንቀቅልህ፤ ከዚህ በላይ ልፍራህ። t.me/abdu_rheman_aman t.me/abdu_rheman_aman

  • 8 авг.1 75011

    በዚህ እድሜ ይሄን ማድረግ አለብህ፣ በዚህ እድሜ ደግሞ እዚህ መድረስ አለብህ የሚባል ቋሚ የህይወት ህግ የለም። እነ እከሌ በሆነ የእድሜያቸው ወሰን ላይ የሆነ ነገር ስላሳኩ ወይም ስላደረጉ፣ አንተም ማድረግ አለብህ ማለት አይደለም። ሁላችንም አንድ አይነት የህይወት መስመር የለንም፤ በተመሳሳይ እድሜ ላይም ብስለትና ክህሎት አይኖረንም። ዕጣ ፈንታችንም አንድ መልክ የለውም። ቁም ነገሩ ተጨባጭህ በፈቀደልህ የእድሜህ ወሰን ላይ ማድረግ ያለብህን ማድረግህ እንጂ ቁጥሩ አይደለም። لكل أوان قطاف، ولكل شيء إوان t.me/abdu_rheman_aman t.me/abdu_rheman_aman

  • 8 авг.1 89426

    ማፅናናት የአባት ነው !!

  • 7 авг.1 87114

    ግብፃዊው ፀኃፊ አህመድ ኻሊድ ተውፊቅ እንዲህ ይላል ፦ " እንደነዛ ሲናደዱ ምግብ እንደማይበሉት ጅሎች አይደለሁም ...በዙሪያዬ እየተከሰተ ባለው ጉዳይ የምበላው ምግብ  ምን ያገባዋል ? " ይላል እና ዝም ብላቹህ ጨጓራችሁን አትላጡ ፤ እየበላቹህ ለማለት ነው !! t.me/abdu_rheman_aman t.me/abdu_rheman_aman

  • 5 авг.2 36311

    አበባም ይሁን ድንጋይ ፣ በግድ እስካሸከሙን ድረስ ያው ሸክም ነው። - ከመፀኃፍ ዓለም። t.me/abdu_rheman_aman t.me/abdu_rheman_aman

  • 5 авг.2 51314

    እኔም ተስፋን እወዳለሁ። እንደ ረሱል(ሰለዋቱ ረቢ ዓለይሂ)። ሁሉም ሰበቦች አልቀው እንኳን ቢሆን  አሁንም ተስፋ ማድረግ። ምን መሰለህ? ነገ የሚባለው ቀን የራሱን ብርሃን ይዞ ነው የሚወለደው። አይደል?  ሰማይ እንቅብ - ምድር የምታንቀረቅብ ጠባብ ሰፌድ በሚሆንብን ሰዓት እንኳን   ተስፋ ማድረግ። ኢስላምም ይህን ነው የሚያስተምረው። t.me/abdu_rheman_aman t.me/abdu_rheman_aman

  • 3 авг.2 57921

    በውጭ ያለው ቅዝቃዜ በውስጣችን የሚነደውን እሳት ሊያጠፋው አይችልም። አንዳንዴ በጭንቅላታችን ውስጥ የሚንቀለቀለው ኃሳብ ... ሙሉ ዓለምን የሚያቃጥል ያህል ይሰማናል። ምን ተሰማቹህ ?

  • 3 авг.2 67715

    አንዳንዴ … መፃፍ የማይጨርሳቸው ዕውነቶች፣ ማንበብ የማይተረጉማቸው ታሪኮች፣ መስማት የማይለውጣቸው ንግግሮች አሉ። እንዲሁም ብቻ ለማወቅ የምናውቃቸው … እንደሚነጋ እንጂ፤ ለምን እና እንዴት እንደሚነጋ ማን ያውቃል ? t.me/abdu_rheman_aman t.me/abdu_rheman_aman

  • 3 авг.2 21414

    ቢረዝምም መንገዴ ግልፅ ይሆን ዘንድ፣ ቢዘገይም ምርጫዬ ሰላም ይኖረው ዘንድ እመኛለሁ። ህይወት መዕና ሲኖረው ደስ ይላል። በማያበስሉ የጊዜ ልምምዶች ውስጥ ቆይቶ አመድ አፋሽ መሆን እንዴት ያስጠላል?! … ትርጉም የሚኖረው ህይወት ግን ምንድን ነው? … አንድም ለአላህ የተሰጠ፣ ሁለትም ለቤተሰብና ለወዳጅ የተኖረ አይደል? … በእነዚህ ውስጥ ነው ሩህ የሚጠግበው። ከዚያ በኋላ ሩህ አካልን ቢለይም ግድ የለኝም። ለዚህ ሳንበቃ ወደ ቀብር አታስጠጋን፤ አላሁመ አሚን! t.me/abdu_rheman_aman t.me/abdu_rheman_aman

  • 2 авг.4 53726

    የህይወት እንቅፋቶችን አትጥላቸው።  እነርሱ ላንተ ብለው የተፈጠሩ ናቸው። የህይወትን ጥፍጥና የምትገነዘበው በነርሱ ውስጥ ነው። እንቅፋቶች ባይኖሩ የህይወትን ምንነት መረዳት ይከብድህ ነበር። አስተውል! ጨለማ ሳይኖር የብርሃንን ጥቅም መረዳት ይርቅሃል። t.me/abdu_rheman_aman t.me/abdu_rheman_aman

  • 1 авг.2 76323

    ደግነትህ ወሰን ካጣ ጥቅምህ እንጂ ማንነትህ አይታይም፤ ልብህን ሳይሆን እጅህን ለሚወዱ ሰዎች ወሰን ይኑርህ !! t.me/abdu_rheman_aman t.me/abdu_rheman_aman

  • 30 июл.3 14222

    “መቼም ቢሆን ምሉዕ ነገር አታገኝም። ጎዶሎ የሆኑ ነገሮችን ታገኝና  ወደህ በመቀበል ይሟላሉ።” لو كنت كاملا لما كنت بشرا، والنقص فيك هو جمالك t.me/abdu_rheman_aman t.me/abdu_rheman_aman

  • 29 июл.3 81712

    አፊያ ያጣ ሰው ዱዓው ሁሉ አፊያ ብቻ መሆኑን ስታይ ምን ያህል አላህ እንደታገሰን እና ኒዕማውን እንደለገሰን ይገባሀል!። አል-ሐምዱ ሊላህ t.me/abdu_rheman_aman t.me/abdu_rheman_aman

  • 28 июл.3 51511

    ከራሱ አልፎ መላ ቤተሰቡን በመኃላ እየረገመ የዑለማኦችን ስም በማጠልሸት የሚፈለግ ርካሽ ትኩረት፣ መጨረሻው የራስን አኺራ ማበላሸት እና በገዛ ድፍረት መዋረድ ብቻ ነው። የነቢያትን ወራሾች ክብር ማነወር በዒልም ስም የሚደረግ የሐዳዲዮች የጥፋት መርዝ ነው። ​ስንቱን  ካፊር እና ሙብተዲዕ አለ በረቢ!

نَـحْـنُ أَبْـنَاءُ السَّلفِــيِّينْے — tgindex